29/04/2026
በባህር ዳር ዙሪያ የታቀደው የጥፋት ሴራ በመከላከያ ሠራዊት መከነ
በአንደሳ ከተማ በተደረገ መብረቃዊ ኦፕሬሽን የተለያዩ ተተቸኳሽ መሳሪያዎች በመከላከያ ተማረኩ።
ከሻዕቢያ የተላከውና በህወሓት በኩል ለፋኖ የቀረበዉ የተለያዩ ጦር መሳሪያ ክልሉን በተለይም በባህርዳር ዙሪያ አንደሳ ከተማ
ተጨማሪ ቀዉስ ዉስጥ እንዲከት ታስቦ ቢሆንም በጀግናው የመከላከያ ሰራዊት በተፈፀመ ድንገታዊ አፕሬሽ ሙሉ ለሙሉ ተማርኳል።
30/03/2026
ሰላም ያሸንፋል!
የሰሜን ወሎ ላሊበላ አካባቢ የሚንቀሳቀሰው ፋኖ የኮር አዛዥ የነበረው ፍቅሬ ሙልዬ ከመንግስት ጋር ውይይት አድርጎ የሰላም አማራጭን ተቀብሎ ከነትጥቁ ገብቷል። በዘረፋ እና በባንዳነት መኖርን አማራጭ የደረገው ጽንፈኛ ቡድን እየፈረሰ ነው።
30/03/2026
በሰላማዊው ህዝብ ላይ ስጋት የነበረው ጸሃዬ ወልዴ በጸጥታ ኃይሎች እርምጃ ተወሰደበት።
የአማራን ህዝብ ሰላም የነሳው ጽንፈኛ ታጣቂ ቡድን አይቀጡ ቅጣት እየተቀጣ ነው። በሸዋ አካባቢ የሚንቀሳቀሰውን ጽንፈኛ ታጣቂ ቡድን ሲመራ የነበረው 50 አለቃ ጸሃዬ ወልዴ የተባለ ሽፍታ በጸጥታ ሀይሎች ላይመለስ ተሸኝቷል።
05/03/2026
በትግራይ ክልል የሠራተኞች የደመወዝ መዋጮ ትዕዛዝ ቅሬታ አስነሳ»
በትግራይ ክልል የሚገኙ ዋና ዋና ተቋማት—ኢትዮ ቴሌኮም፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የገቢዎች ቢሮ እና አራት ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ—ሠራተኞቻቸው ደመወዛቸውን እንዲለግሱ የሚጠይቅ መመሪያ ደረሳቸው። የጦርነት ተጎጂዎችን ለማከም እና ተፈናቃዮችን ለመመለስ በሚል በቀረበው በዚህ ትዕዛዝ ቢሆንም ገንዘቡን ሰብስቦ ለጦርነነት ለመጠቀም እንደሆነ የውስጥ ምንጮች ገልጸዋል ። የተቋማቱ አመራሮች የደመወዛቸውን 20% እንዲለግሱና ሠራተኞችም የሚቆርጡትን መጠን በአምስት ቀናት ውስጥ እንዲያሳውቁ ተገደዋል። ይሁን እንጂ ለረጅም ጊዜ ደመወዝ ባልተከፈለበትና የኑሮ ውድነት በጸናበት ወቅት የቀረበው ይህ "የግዴታ" መዋጮ በሠራተኛው ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታና ስጋት ፈጥሯል።
24/02/2026
የዓለምጸሃይ ሽፈራው የዘረፋና የቤተሰባዊ ሙስና መረብ ሲጋለጥ"
የአዲስ አበባ የብልጽግና ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ እና የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ዓለምጸሃይ ሽፈራው ዘመዶቿን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መዋቀር ውስጥ ሰግስጋ የሌብነት መዋቅር በመዘርጋት እንዲሁም ባለቤቷን በመሬት ማሻሻጥ ስራ ላይ በማሰማራት በቢሊዮን የሚቀጠር ሃብት በህገወጥ መንገድ ማከማቸቷ ተደረሰበት። ዓለምጸሃይ ሽፈራው የቦሌ ክፍለከተማ ጽህፈት ቤት ሃላፊ በነበረችበት ወቅት በሺህ ሄክታር የሚለካ መሬት ‘ሰነድ አልባ’ በሚል በመያዝ የመሬት ማሻሻጥ ስራ ላይ ባሰማራችው ባለቤቷ አማካኝነት መቸብቸቧ ተደርሶበታል። በዚህ የመሬት ችብቸባ ህገወጥ ተግባር ያገኘችውን በቢሊየን ብር የሚቆጠር ሃብት በባለቤቷ አማካኝነት በጥቁር ገበያ ወደ ዶለር በመቀየር ከሃገር ማሸሿን የሚያመለክቱ መረጃዎች ተገኝተዋል። ይህች የተሰጣትን አደራ በልታ በህዝብ ላይ እንደ መዥገር ታጠብቃ ስትዘርፍ የነበረች ሴት ሳይውል ሳያድር ካሃለፊነቷ ተነስታ በህግ መጠየቅ አለባት!
24/02/2026
የመሬት ዘረፋና የዶላር ሽሽት የአመራሯ የሙስና ቅሌት!
ስልጣንን ያለአግበብ በመጠቀም በህገወጥ መንገድ የከበሩ ሰዎች በህግ ተጠያቂ ሊሆኑ ይገባል። የቀድሞ የቦሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ፣ የአሁን የአዲስ አበባ ብልጽግና ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊና የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ዓለምጸሃይ ሽፈራው በመሬት ሃብት ዘረፋ ላይ ተሰማርታ እንደነበረ የሚያረጋግጡ የሰነድ ማስረጃዎች ተገኝተዋል። ዓለምጸሃይ ሽፈራው ሰነድ አልባ በሚል ሸፋን በብዙ ሺህ ሄክታር የሚለካ መሬት መያዟ እና በህገወጥ የመሬት ሽያጭ እና ድለላ ስራ ላይ ባሰማራችው ባለቤቷ አማካኝነት በቢሊየን በሚቆጠር ብር መቸብቸቧን የሚያሳዩ የሰነድ ማስረጃዎች ተገኝተዋል። በዘረፋ ያገኘችውን ሃብት በጥቁር ገበያ በዶላር መንዝራ ከሃገር እንዳሸሸችም ታውቋል። ብዙዎች “የዚህ አይነት ሴት እንዴት ወደ ሃላፊነት ልትመጣ ቻለች?” የሚል ቁጭታቸውን እየገለጹ በአስቸኳይ ከሃላፊነ ት እንድትነሳ እየጠየቁ ነው። ከሃላፊነት መነሳት ብቻ ግን አይበቃም፤ በህግም መጠየቅ አለባት!
18/02/2026
ሕወሓት ሕዝቡን በረሃብ አለንጋ እየገረፈ የዓለምን ትኩረት
ለመሳብ መሞከሩ የጭካኔ ጥግ ነው።