29/10/2025
“ማንበብና መጻፍ ነዉ ሱሴ፤ ሌትም ቀንም አልመርጥም፡፡ የምተኛዉ ረጅም እንቅልፍ ከአራት ሰዓት አይበልጥም፡፡ ከፍተኛ የገንዘብ አቅም ቢኖረኝ ብዬ ተመኝቼ አላዉቅም፣ ቢኖረኝ ግን በሁሉም ክልሎች ዘመናዊ ቤተ መጻሕፍት አስገነባለሁ፡፡ ‹አንብብ-አንብቢ-አንብቡ-እናንብብ› በሚል መርህ ትዉልዱን ማነጽ ተግባሬ ይሆን ነበር” #ደራሲና #ጋዜጠኛ ዘነበ ወላ🙏🏼🙏🏼🙏🏼
28/10/2025
When they ask me what’s home I said it’s “እናት”
26/10/2025
እኔምለው?
የሄደ ተወቃሽ
የጠበቀ ታጋሽ
የሄደማ አጥፊ
በዳይ ፍቅርን ገፊ
ያስኬደስ ምንድን ነው?
ትእግስት የሚያሳጣው
መቆየት እንዳይችል
እንዲሄድ ያረገው አሱስ ግን ምንድን ነው?
@ሕሊና ሽፈራው
26/10/2025
#መልሕቅ
መልሕቅ ማለት መርከብን ከማዕበልና ከወጀብ የሚታደግ የመርከቧ አለኝታ ማለት ነው። በዕብራውያን መልእክት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምእመናን መልሕቅ ተብሏል።
“ይህም ተስፋ እንደ ነፍስ መልሕቅ አለን፤ እርሱም እርግጥና ጽኑ የሆነ ወደ መጋረጃውም ውስጥ የገባ ነው፤ በዚያም ኢየሱስ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ሊቀ ካህናት የሆነው ስለ እኛ ቀዳሚ ሆኖ ገባ” (ዕብ. 6፡19)።
26/10/2025
“በትልቁ አስብ በትንሹ ጀምር!”
ጋሽ ዘነበ ወላ🙏🏼
25/10/2025
መፅሐፍ ላይ ያለ አንድ የሞት ፍርድ የሚጠባበቅ ፍርደኛ ገፀ ባህርይ ነበር።
ከስቅላቱ አንድ ቀን በፊት ስፖርት ይሰራል! ምን እያደረግክ ነው ቢሉት “ጤናዬን እየጠበቅሁ ነው አለ አሉ! ማምሻም እድሜ ነው!
25/10/2025
“ሆድ ድንጋይ እበላለሁ ቢል ጉሮሮ ማን ቢያሳልፍህ”😏
23/10/2025
ገንዘብን ለማግኘት ጠንካራ ሰራተኛ እና ሃቀኛ መሆን አለብህ is a complete scam.
ተብላችኋል!
22/10/2025
God uses your lowest times to create the highest version of you. Hang in there 🩷
22/10/2025
"ቀኑ እንዴት ይመሻል ያንን ሳናነሳ"
(በእውቀቱ ስዩም)
አዝማሪ ወርቄ (ሻምበል ወረቀት) እንዲህ ይል ነበር፤
“ቢናገሩ አፈኛ፤
ዝም ቢሉ ሞኝ
ቢወፍሩ ዝሆን፥ ቢቀጥኑ ትንኝ ‘
አወይ ሰው! አወይ ሰው! ሰው አስቸገረኝ”
ካዝማሪው የተረፈውን እነዲህ መዘርዘር ይቻላል-
ብትጋብዝ “ አባካኝ “ ትባላለህ- ብትቆጥብ “ ቁዋጣሪ” - ብታሞግስ “ አሽቃባጭ፥- ብትተች” አቃቂረኛ- ብትቀመቅም “ሰካራም” ባትቀመቅም “ አብሿም”- ሴቶች ቢቀርቡህ “አተራማሽ -የሴት ድሮን” ‘ - ሌጣህን ብትሆን “ስልብ “ ወይም “ ጌ”
ሸሸግ ብትይ “ ምነው ጠፋሽ “ - ብቅብቅ ብትይ” ምነው እዩኝ እዩኝ አበዛሽ “ - ባያምርብሽ “አመዳም “ -ቢያምርብሽ “ፊልተራም” ወይም “ዱቄታም” -ብትጨምቺ “ አንገት ደፊ አገር አጥፊ፤ “ ነጻ ብትሆኝ ‘ ሸሌ”
እንደ መካሪ ሲቃጣኝ እንዲህ እላለሁ-
በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ብትገኝ ከሰዎች ምዘና እና ካስተያየት አታመልጥም፤ የሚመዝን ማጉደሉ አይቀርም፤ ዠለስ! እንዳመጣጡ ኑር፤ ዠለሲት እንደፍጥርጥሩ ኑሪ፤ ልብሽን ተከተይ፤ ህግ እስካልጣስህ ድረስ ፥ ሰዎችን እስካልጎዳህ ድረስ ማድረግ የሚገባህን ከማድረግ አትቆጠብ፤
የሆነ ዘመን ላይ አንድ ባላባት ካድዋ ዘመቻ ተመልሰው በህዝብ ፊት ሲፎክሩ ደመቅ ያለ ፈስ አመለጣቸው ፤ ነዋሪውም በታላቁ ዘመቻ ላይ፥ አራት ጣልያን መግደላቸውን ቸል ብሎ ለአራት ሰኮንዶች ያክል አየር ላይ በቆየው ፈሳቸው ዙርያ በማውራት ተጠመደ ፤ ባላባትየው ለህዝቡ ጥሩ ነገር በመስራት ገጽታቸውን ለመገንባት ወሰኑ ፤ አስር በሬ አርደው የአገሩን ሰው ጠርተው አበሉት፤ "እኒያ አስር በሬ ያበሉት ጌታ" እየተባሉ እንዲነሱ ተመኝተዋል፤
ከተበላ ከተጠጣ በሁዋላ አንዱ አዝማሪ ብድግ አለና እንዲህ አቀነቀነ፥
“እንኩዋን አስር በሬ ቢታረድ ሰላሳ
ቀኑ እንዴት ይመሻል ያንን ሳናነሳ🙂
በውቀቱ ስዮም
15/10/2025
የሰውን ሳያጣጥሉ የራስን ማሞገስ እንደሚቻል ንገሩልኝ እስቲ!🙄