08/10/2025
አዲስ አበባ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ፌደሬሽን Addis Ababa International Taekwon_Do Federation
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from አዲስ አበባ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ፌደሬሽን Addis Ababa International Taekwon_Do Federation, Sports Team, Addis Ababa.
08/10/2025
12/09/2025
የአባይ ግድብን መጠናቀቅ ምክንያት በማድረግ 28 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የስፓርት ፌስቲቫል ሊካሄድ ነው
መስከረም 02 ቀን 2018ዓ.ም ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የታላቁ የህዳሴ ግድብ መጠናቀቁን ምክንያት በማድረግ መነሻውን ሽሮ ሜዳ መድረሻውን ሲኤምሲ አፍሪካ ኮንቬሽን ሴንተር ያደረገ የከተማው ወጣቶች እና የስፖርት ቤተሰቦች የሚሳተፉበት የስፖርት ትርኢት እንቅስቃሴ መስረም 3 2018 ዓ/ም እንደሚያካሂድ ተገለጸ፡፡
36ቱም ፌደሬሽኖች በሚሳፉበት የስፖርት ፌስቲቫልና ትርኢት 28 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን 14 መዳራሻዎች እንዳሉት ያወሱትየማህበረሰብ አቀፍ ስፖርት ማስፋፋያና ተሳትፎ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እንግዳወርቅ ዳንኤል በአምስት ጣቢያዎች የሰርከስ ትርኢት የማርሻል አርት ስፖርት እና የባህል ውዝዋዜ እንደሚካሄድ አመላክተዋል፡፡
በዝግጅቱ ላይ ብስክሌተኞች፣ ስኬተሮች ፈረሰኞች ፣ ሞተረኞች ፣ የማርሻል አርት ቤተሰቦች እና ሰርከሶች በጎዳና ላይ ትርኢቱ የሚሳተፉ ሲሆን የአባይ ግድብ በመጠናቀቁ የተሰማቸውን ደስታ የሚያበስሩ ልዩ ልዩ መልዕክቶች እንደሚተላለፉ ይጠበቃል።
ስፖርታዊ ትርኢት እና የጎዳና ፌስቲቫሉ አራት ኪሎ፣ አድዋ ሙዚየም፣ መስቀል አደባበይ፣ ቦሌ ድልድይ፣ መገናኛ እና ሲኤምሲ ኮንቬሽን ልዩ ልዩ ትርኢቶች በቅንጅት የሚቀርቡባቸው ስቴሽኖች መሆናቸው ተመልክቷል፡፡
28 ኪሎ ሜትር በሚሸፍነው የጎዳና ላይ የስፖርት ትርኢት መነሻውን ሽሮ ሜዳ በማድረግ እስከ አራት ኪሎ፣ በራስ መኮንን ድልድይ በማድረግ አድዋ መታሰቢያ ሙዚየም፣ ቸርቸል ጎዳና፣ ብሔራዊ ቴአትር፣ መስቀል አደባባይን በማቆራረጥ ቦሌ ደንበል፣ ኤርፖርት በማድረግ መገናኛ በመድረስ ሳህሊተ ምህረት አድርጎ አፍሪካ ኮንቬሽን ሴንተር እንደሚጠናቀቅ ተመልክቷል፡፡
ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎች ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን
👍👍👍 ፌስ ቡክ ገጽ:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100069054105219
👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል: https://t.me/youthsport2014
👍👍👍 you tube https://www.youtube.com/channel/UC0CARW3IdFaPlZ980VITn5Q
👍👍👍ትዊተር :- https://twitter.com/SportYout79296
👍👍👍ቲክቶክ
https://vm.tiktok.com/ZMYR8WTs8
21/08/2025
12/08/2025
ቢሮው በ2017 በጀት አመት የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የዘርፉ ተቋማት እውቅና ሽልማት አበረከተ
ነሐሴ 6 ቀን 2017 ዓ/ም ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የዘርፍ ተቋማት እና ባለሙያዎች እውቅና እና ሽልማት መርሃ ግብር አካሄደ
ለተቋማት እና ለባለሙያዎች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክት ያስተላለፉት የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በላይ ደጀን ቢሮው በ2017 አፈጻጸም የተሻለ ዉጤት እንዲያስመዘገብ ሁሉም የተቋሙ መዋቅር ትልቅ ሚና እንደነበረዉ አስታውሰው በቀጣይም ስፖርትን ለማስፋፋት የወጣቱን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቅንጅት መሰራት ይገባል ብለዋል።
በአዲሱ በጀት ዓመት የስፖርት ልማቱን ለማፋጠን እና የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቁጭት ልንሰራ ይገባል ያሉት አቶ በላይ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ደረጃቸውን ለማስጠበቅ ዝቅተኛ ያመጡ ተቋማት የላቀ ደረጃ ለማምጣት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል
በፌዴሬሽኖች በተካሄደው ምዘና ስፖርት ለሁሉም ኮሚቴ ቀዳሚ ሆኖ ሲያጠናቅቅ አዲስ አበባ ኢንተርናሽናል ቴኴንዶ 2ኛ እና ቦክስ ፌዴሬሽን 3ኛ በመሆን የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል
31/07/2025
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Website
Address
Opening Hours
| Monday | 09:00 - 17:00 |
| Tuesday | 09:00 - 17:00 |
| Wednesday | 09:00 - 17:00 |
| Thursday | 09:00 - 17:00 |
| Friday | 09:00 - 17:00 |