Ebroo Football/ኢብሮ እግር ኳስ

Ebroo Football/ኢብሮ እግር ኳስ

Share

በእግር ኳስ ውጤት ልንርካ የምንችለው ታዳጊዎች ላይ ስንሰራ ብቻ ነው።ትኩረት ለታዳጊዎች!

16/12/2025
02/12/2025

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉን አረጋገጠ፡፡

ቡድኑ ድሉን ያረጋገጠው ዛሬ ከኬንያ አቻው ጋር በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታድየም ባደረገው ጨዋታ 3ለ0 በማሸነፉ ነው፡፡

የማሸነፊያ ግቦቹን የውድድሩ ክስተት ዳዊት ካሳው እና አምበሉ ቢንያም፣ብሩክ አስቆጥረዋል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ከ22 ዓመታት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ውድድር ተመልሷል፡፡

የአፍሪካ ከ17 ዓመት በታች የዋንጫ ውድድሩ በሞሮኮ አስተናጋጅነት ይካሄዳል፡፡

ዛሬ ከቀኑ 9፡ 30 ላይ ዩጋንዳ እና ታንዛኒ የሴካፋ ከ17 ዓመት በታች የዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

Photos from Ebroo Football/ኢብሮ እግር ኳስ's post 28/11/2025

17 ቀይ ካርድ የተመዘዘበት የደቡብ አሜሪካ ጨዋታ

በደቡብ አሜሪካ ቦሊቪያ በተደረገ ጨዋታ በተነሳ ብጥብጥ 17 ቀይ ካርድ ሲመዘዝ ጨዋታውን ለማረጋጋት ፖሊስ አስለቃሽ ጭስ ተጠቅሟል

በብሉሚንግ እና ሪል ኦኩሮ መካከል በተደረገው ጨዋታ ሲሆን ፀቡ የተነሳው ከሁለቱም ቡድኖች 11 ተጨዋቾች በቀይ ካርድ ወጥተዋል

ከሁለቱም ክለቦች 6 የአሰልጣኝ ስታፍ አባላትም ቀይ ካርድ አይተዋል

ቀይ ካርድ ከተመለከቱ ተጨዋቾች መካከል 6 ያህሉ ሙሉ ውድድር አመቱን መቀጣታቸው ተገልጿል

Photos from Ebroo Football/ኢብሮ እግር ኳስ's post 25/11/2025

የኤፍ.ኤ ካፕ ዋንጫም ወደ ኢትዮጵያ መጣ

| "ሺ ዊንስ" የተሰኘ በአይነቱ ልዩ የሆነ የእግር ኳስና የሴቶችን አቅም ማጎልበት ላይ ያተኮረ ፕሮግራም ተጀመረ።

የኢንግሊዝ ኤምባሲ፣ ከአዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ እና ኤን ዜድ ኮምኒኬሽንስ ጋር በጋራ ባሰናዱት መርሃግብር ላይ ተወዳጁ የእንግሊዝ የኤፍ ኤ ካኘ ዋንጫ ለህዝብ እንዲታይ የፊታችን ቅዳሜ እና እሁድ በሴቶች አደባባይ የእግር ኳስ ሜዳ ላይ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ ለተመልካቾች ክፍት እንደሚደረግ ተገልጿል።

ለአምስት ቀናት በሚካሄደው በዚህ ፌስቲቫል በአዲስአበባ እና ከአዲስ አበባ ውጪ ያሉ ወጣት ሴቶችን በማሰባሰብ በእግር ኳስ ውድድሮች ፣በአመራርነት፣ራስን በማብቃት ላይ ስልጠና ይሰጣል በተያያዘም የስልጠና ሞጁል ለሰልጣኞች በአማርኛ ተዘጋጅቶ ተስጥቷል፡፡

አርአያ የሚሆኑ ሴቶችም ተሞክሯቸውን የሚያካፍሉበት በዚህ ፕሮጀክት ከ10ሺህ በላይ ሴቶችን ለመድረስ ታቅዷል፡፡

በዚህም የአመራር ብቃታቸው እንዲጎለብት፣ በራስ መተማመናቸው እንዲጨምር በማድረግ በግልና በስራ ህይወታቸው አዲስ በሮች እንዲከፈቱ የሚያደርግ ይሆናል፡፡እያንዳንዷ ሴት የምታልመውን ሁሉ ማሳካት እንደምትችል የሚያበረታም ይሆናል፡፡

የእግርኳስ ውድድሩ ስምንት ቡድኖችን የሚያካትት ሲሆን በዚህ አሰልጣኞች ባለተሰጠኦችን እንዲለዩ የሚያስችላቸው ይሆናል፡፡

ቡድኖቹ የአስፈላጊ ቁሳቁስ ልገሳ የሚደረግላቸውም ይሆናል፡፡ ለዚህም ዓላማ ከሀገረ እንግሊዝ በ2013 ከዊጋን አትሌቲክ ጋር የኤፍ.ኤ ካፕ ሻምፒዮን በሆነው ኤመርሰን ቦይሴ የተመራ 3 ኢንተርናሽናል የአሰልጣኞች ቡድን አዲስ አበባ ገብቷል።

የአሰልጣኝነት ስልጠናዎችን ይካሄዳሉ፣ ከ17 አመት በታች ያሉ ወጣት ሴት ባለተሰጥኦዎችን የመለየት ስራም የሚካሄድ ይሆናል፡፡

ሺ ዊንስ እሷ ስታሸንፍ እኛም እናሸንፋለን በማለት በኢትዮጵያ የጾታ እኩልነት ፣ የወጣቶች አቅም መጎልበትና የሴቶች ስፖርት እድገት ቁርጠኝነት ላይ አበክሮ ይሰራል፡፡

24/11/2025

ሩሲያ ከአለም ዋንጫው የተሰናበቱ ሀገራትን ሰብሰባ ፊፋ የማያውቀው ሌላ የአለም ዋንጫ ልታዘጋጅ እንደሆነ እየተነገረ ነው።እነዚህ ከ8-12 የሚደርሱ ሀገራትም ሩሲያ ልደግሰው ባሰበችው አለም ዋንጫ እንደሚሳተፉ ተገልፆል።

🇷🇺 Russia (hosts)
🇨🇳 China
🇨🇲 Cameroon
🇳🇬 Nigeria
🇷🇸 Serbia
🇨🇱 Chile
🇬🇷 Greece
🇵🇪 Peru
🇻🇪 Venezuela

23/11/2025

ራሱን ለመከላከል 6 ሚሊዮን ብር ውሻ የገዛው አይዛክ!🥹

: የእንግሊዙ ክለብ ሊቨርፑል ለኒውካስል ዩናይትድ 125 ሚሊዮን ፓውንድ ከፍሎ ስዊድናዊውን አጥቂ አሌክሳንደር አይዛክን የግሉ ማድረጉ ይታወቃል ። ኒውካስል ስውድናዊ የፊት መስመር ተጫዋቹን የመሸጥ ፍላጎት ያለበረው በመሆኑ ፤ ብዙ ውዝግብ ያስነሳ ጉዳይ እንደነበር ይታወሳል ።

በወቅቱ የ26 ዓመቱ ስዊድናዊ አጥቂ ክለቡ እንዲለቀው በግልጽ እስከመጠየቅ ደርሷል ። ኒውካስልም አይዛክን ለማቆየትበተጫዋቹ ላይ የ150 ሚሊዮን ፓውንድ ዋጋ በመለጠፍ ፤ አይዛክ ወደ ሌላ ክለብ እንዳይሄድ ለማድረግ ጥረት አደረጉ ።
ልቡ የሸፈተው አሌክሳንደር አይዛክ ግን በማግፓይሶቹ ቤት መቆየት እንደማይፈልግ በግልጽ እስከመናገርም ደፈረ ።

ክለቡ እንዲለቀው ጫና ለመፍጠርም በኒውካስትል የቅድመ ውድድር ዝግጅትም ሆነ በክለቡ የፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያ ሁለት ጨዋታዎች እስካለመሳተፍ ደረሰ ።

በብዙ ውዝግብ ሊቨርፑል ስውድናዊውን የፊት መስመር አጥቂ በእጁ ሊያስገባው ችሏል ። ነገርግ ግን በአሌክሳንደር ኢዛክ ውሳኔ እና ድርጊት የተበሳጩ የኒውካስል ደጋፊዎች በተለያዩ መልክ ቁጣቸውን ሲገልጹ ቆይተዋል ።

ዛሬ ላይ የደጋፊዎቹ ቁጣ ወደ ግድያ ማስፈራሪያ እና ዛቻ ማደጉን ተሰምቷል ። በተጫዋቹ ላይ የግድያ ዛቻ የሚያቀርቡት አካላት የኒውካስል ደጋፊዎች ብቻ አይደሉም ተብሏል ።

በ2026 ለሚደረገው ዓለም ዋንጫ ሀገሩ ስዊድን የማለፍ እድሏ ጠባብ በመሆኑ ፤ ያኮረፍ የሀገሬው ዜጎች ማስፈራሪያውን መቀላቀላቸው ተነግሯል ። ይህም ተጫዋቹን ከፍተኛ ጫና ውስጥ የከተተው ሆኗል ።የ26 ዓመቱ ወጣት ከሁለት ወገን በርካታ ማስፈራሪያዎች በማህበራዊ ድህረ ገፅ እየደረሱበት ይገኛል ።

በሁለት በኩል እንድ ድፎ ዳቦ እሳት እየነደደበት በመሆኑ የራሱ እና የቤተሰቡ ደህንነት አደጋ ላይ መውደቁ ተሰምቶታል ። ከኤርትራዊ ቤተሰቦች የተገኘው ኮከብ ከሜዳ ውጪ በቤተሰቡ እና በእሱ ላይ እየደረሱበት ያለውን የግድያ ማስፈራሪያ ለመከላከል እንዲጠቅመው የጥበቃ ውሻ መግዛቱ ተሰምቷል ።

አሌክሳንደር ኢዛክ 30ሺ ፓወንድ ማለትም 6 ሚሊዮን 36 ሺህ 93 ብር በማውጣት የጥበቃ ውሻ ለመግዛት ተገዷል ። የጥበቃ ውሻው ከደጋፊዎች የሚደርስበት ዛቻ ወደ ጥቃት ካደገ ራሱን መከላከል እንዲያስችለው መሆኑም ተነግሯል ።
በዘንድሮ የውድድር ዓመት ሊቨርፑልን የተቀላቀለው ስዊድናዊው ኮከብ ከክለቡ ጋር የ6 ዓመት ኮንትራት መፈራረሙ ይታወሳል ።

በ2022 ከሪያል ሶሴዳድ ወደ ኒውካስል የተዛወረው ኢዛክ በማግፓይሶቹ ቤት በነበረው ቆይታ በ109 ጨዋታዎች 62 ጎሎችን ሲያስቆጥር 11 ግብ የሆኑ የመጨረሻ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል። በፕሪሚዬር ሊጉ ብቻ 54 ጎሎችን በስሙ ያስመዘገበው ተጫዋቹ ኒውካስል ባለፈው ዓመት በካራባው ካፕ ፍፃሜ ሊቨርፑልን በማሸነፍ ከ70 ዓመታት በኋላ ዋንጫን ሲያነሳ አስተዋጽኦው ከፍተኛ እንደነበር አይዘነጋም።

22/11/2025

ሴኔጋላዊው የእግር ኳስ ኮከብ ሙሉ
መንደር ዳግም እየገነባ ነው

| ታዋቂው የጣልያን የስፖርት ጋዜጠኛ ፋብሪዚዮ ሮማኖ እንደተናገረው፤ ሴኔጋላዊው የእግር ኳስ ኮከብ ሳድዮ ማኔ፣ በሴዲዮ ክልል ውስጥ የምትገኘውን የትውልድ ቀዬውን - ባምባሊን - እየቀየራት ነው፡፡

በእቅዱ መሰረት በቀዬው ከሚገነባቸው መሰረተ ልማቶች መካከል፡-

- አዲስ ሆስፒታል

- ትምህርት ቤት

- ሙሉ 4G ኔትዎርክ

- ፖስታ ቤት

- ነዳጅ ማደያ

- ስታዲየም --- ይገኙባቸዋል፡፡

በተጨማሪም ሳድዮ ማኔ ለእያንዳንዱ ነዋሪ በየወሩ 70 ዩሮ እንደሚሰጥ ተዘግቧል፡፡ በዚህም ሴኔጋላዊው የእግር ኳስ ኮከብ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ህይወት ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ እንደሚፈጥር ነው የስፖርት ጋዜጠኛው የገለጸው፡፡ #አዲስ አድማስ

20/11/2025

ለሮናልድ ትልቅ ትርጉም ያለው የኦቫል ኦፊስ ጉብኝት

በማዴራ በአስከፊ ድህነት ያሳደጉት ፖርቹጋላዊ ገበሬ አባቱ ለቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሮናልዶ ሬጋን ባላቸው የተለየ ፍቅር የተነሰ ልጃቸውን ሮናልዶ ሲሉ ሰየሙት

ከ 40 አመታት በኋላ ልጃቸው ክርስቲያኖ ሮናልዶ በወቅቱ የሚወዱት ፕሬዚደንት ሮናልዶ ሬጋን ስራውን በሰራበት ተመሳሳይ ቤት የአሜሪካውን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አግኝቶ አነጋገራቸው

ወላጅ አባቱ በህይወት ኖረው አብዛኛውን የክርስቲያኖ ሮናልዶ ስኬት እና ዝና መመልከት አልቻሉም ይሄ የሁልጊዜ ቁጭቱ መሆኑን ሮናልዶ ሁልጊዜ ሲያነሳ ይሰማል።

18/11/2025

😓🥰ይህ ልብ የሚነካ ምስል በእውነት ሳያስተዋሉ እንዲያልፍ መፍቀድ የለብኝም። ይህ ምስል አጭር ቅጽበት ብቻ ሳይሆን ጥልቅ የሰው ልጅ ታሪክ ጭምር ነው። አንድ አባት ልጁን በጉልበቱና በመንፈሱ ዓለምን እንደሚያነሳ ሁሉ በትከሻው ላይ ተሸክሞ ፊታቸው የማይናወጥ ጽናት፣ የማይለካ ፍቅር እና ትከሻውን ለልጁ ደህንነቱ የተጠበቀ የትውልድ አገር አድርጎ የገለጸ የድንቅ ሰው ታሪክን ይተርካል።

ልጁ የመተንፈሻ መሣሪያ በፊቱ ላይ ቢገጠምም እና ከድካም ጋር በየቀኑ የሚያደርገውን ትግል ቢመለከትም፣ ትንሿ ደረቱ ሊይዘው ከሚችለው በላይ የሆነ ህልም እየነካ እንደሆነ ሁሉ የፍላሜንጎ ማሊያውን ለብሶ ፈገግ ይላል። ግጥሚያን ብቻ እየተከታተለ አይደለም... ከሚወደው ዓለም፣ በተስፋ፣ በባለቤትነት እና በደስታ ወደሚሞላው ክለብ እየተጠጋ ነው።

ምክንያቱም እግር ኳስ ስለ ግቦች፣ መዝሙሮች ወይም ስለ መጨረሻው ፊሽካ ብቻ አይደለም፤ ሙሉ ህይወትም ጭምር ነው። የታመመ ልጅ ለማለም ምክንያት የሚሰጥበት እና የደከመ አባት እንደ ተራራ ቆሞ ልጁን ወደሚወደው ነገር የሚያነሳው ጊዜ ነው። ህመሙ ምንም ያህል ከባድ ቢሆን፣ የማይለቅቅ ፍቅር፣ ጓደኝነት እና እቅፍ ውስጥ ነው።

ስለዚህ ይህንን ትዕይንት ችላ ማለት ንፉግነት ነው... ስለ መስዋዕትነት፣ ስለ አባትነት ጀግንነት እና በምላሹ ምንም ሳይጠብቁ በሚሰጥ ልብ ውስጥ የሚቀመጥ ጸጥ ያለ ትምህርት ጭምር ነው!

በባዶ እግሩ እየሄደ ለልጁ ቅያሪ የሚገዛ፣ እየራበው ረሃቡን ችሎ ልጁን የሚያጠግብ፣ ችግሮቹን ብቻው የሚወጣ፣ አጣሁ ደከምኩ ሰለቸኝ የማይል፣ ሳይማር የሚያስተመር፣ ብቻውን ተዋጊና መሪ የሆነ ድንቅ ድንቅ አባቶችም አሉ... አባት ሺህ ዓመት ይኑር🙏🥰✅

አባትነት🥰🙏✅

Football Era

Photos from Ebroo Football/ኢብሮ እግር ኳስ's post 16/11/2025

👉መልካም ዜና!!🙏

👉ባለፈው ዓርብ ህዳር 05/2018 ጃፓን ከ ጋና ጋር ባደረጉት የወዳጅነት ጨዋታ ላይ ጋናዊው የአማካይ መስመር ተጨዋች ፍራንሲስ አቡ ከ ጃፓናዊው ተጨዋች ፓናካ ጋር ተጋጭቶ፣በቀኝ እግሩ ላይ ጥንቱ ተሰብሮ አደገኛ ጉዳት ማስተናገዱ ይታወሳል።

ሆኖም ዛሬ እየወጡ የሚገኙ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት፣ጉዳቱ የከፋ ቢመስልም በጃፓን ቶዮታ መታሰቢያ ሆስፒታል በተደረገለት ቀዶ ጥገና፣የእግሩን አጥንቶች ወደነበሩበት መመለስ መቻላቸውን፣እና ወደ አውሮፓ ከመብረሩ በፊት፣ለተጨማሪ ሳምንታት በዚያው ጃፓን እንደሚቆይ ተገልጿል።

ከቀዶ ጥቀናው በኋላ የተሠራለት ምርመራ እንደሚያሳየው ከሆነ ፣ከ6-8 ወራት ቆይታ በኋላ ወደ ጨዋታ ሊመለስ እንደሚችልም እየተዘገበ ነው።

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Telephone

Address

12
Addis Ababa
ታዳጊዎችላይበመሰራትኳሳችንእናሳድግ