08/01/2026
ለመገናኛ ብዙሃን !
አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳሕሌ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ በመሆን መሾማቸው ይታወቃል። የውሉን ዝርዝር እና አጠቃላይ ጉዳዮች በተመለከተ ሐሙስ ታኅሣሥ 30 ቀን 2018 ዓ/ም በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፅሕፈት ቤት ከቀኑ በ9፡00 ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል።
የመገናኛ ብዙሃን አካላትም በቦታው በመገኘት ጥያቄያችሁን እንድታቀርቡ እና የሚዲያ ሽፋን እንድትሰጡ በማክበር እንጠይቃለን፡፡
19/12/2025
🇺🇬 ኡጋንዳ አዲስ ያስገነባችዉ እና 20,000 ተመልካቾችን የመያዝ አቅም ያለውን የሆይማ ሲቲ ስታዲየምን ታህሳስ 24 - 2018 ዓ.ም በይፋ ታስመርቃለች።
131 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የተደረገበት ይህ ስታዲየም በ2027ቱ የአፍሪካ ዋንጫ የሚደረጉ ጨዋታዎችን ያስተናግዳል።
11/11/2025
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና የሀዋሳ ከተማ ተጫዋች በሆነችው ለምለም አስታጥቄ ላይ ድብደባ የደረሰ መሆኑን ሰሞኑን በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየተዘዋወረ ባለ ቪድዮ ተመልክተናል። በመሆኑም በዚህ ቪድዮ ዙርያ የሀዋሳ ከተማ እግር ኳስ ክለብ በአስቸኳይ ማብራርያ እንዲሰጥ የኢትዮጽያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጠይቋል።
31/10/2025
በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ከኅዳር 6 ጀምሮ የሚከናወነው የሴካፋ ዞን ከ17 ዓመት በታች አፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ውድድር የምድብ ድልድል ይፋ ሆኗል።