Mobappé
Ethio handball for ever
handball family
26/12/2025
የ2018 የኢትዮጵያን እጅ ኳስ ፕርሚየር ሊግ ውድድር ሊጀመር ነው አምና በጥሩ ብቃት ላይ የነበረው የመቀሌ 70 እንደርታ ቡድን የ2018 ይደግመው ይሆን ? እስቲ ነገ ከቅዳሜ 18/04/18 የሚጀመረው ተወዳጁ እጅ ኳስ ከአመት ቆይታ በዋላ ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል የምንመለከት ይሆናል የ2018 አሸናፊ ይገምቱ ማን ሻምፒየን ይሆናል ?
20/12/2025
እንኳን ደስ አለን እንኳን ደስ አላቹ CAHB ኢትዮጵያዊውን ዶ/ር ፍትህ ወልደሰንበትን CAHB ዞን 5 ፕሬዝዳንት ሆነው በድጋሚ ተመረጡ
ካይሮ፣ ግብፅ — የኢትዮጵያ የስፖርት መሪ ፍትህ ወልደሰንበት (PHD) የአፍሪካ የእጅ ኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAHB) ዞን 5 (ምስራቅ አፍሪካ) ፕሬዝዳንት ሆነው በሁሉም የአባል ሀገራት በሙሉ ድምጽ ተመርጠዋል።
ውሳኔው የተወሰደው ታህሳስ 19፣ 2025 ዓ.ም. በካይሮ በሚገኘው ሴንት ሬጂስ ሆቴል በተካሄደው የCAHB ዞን 5 የምርጫ ኮንግረስ ወቅት ነው።
ዞን 5 11 የምስራቅ አፍሪካ አገሮችን ያቀፈ ነው፡ ኢትዮጵያ፣ ግብፅ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ጅቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ኬንያ፣ ሩዋንዳ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያ እና ቡሩንዲ።
ተወካዮቹ ዶ/ር ፍትህ ወልደሰንበትን ለሌላ ጊዜ ከማጽደቃቸው በፊት በዞኑ ውስጥ የተገኙ ስኬቶችን እና የተጀመሩ ተነሳሽነቶችን ገምግመዋል። በኮንግረሱ ላይ ባደረጉት ንግግር፣
CAHB ፕሬዝዳንት ዶ/ር ማንሱሩ የአፍሪካ አንድነት፣ የእጅ ኳስ የጋራ ልማት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ጠንካራ እና የተዋሃደ የአፍሪካ ድምጽን በማቅረባቸው የአፍሪካ አንድነት አስፈላጊነትን አፅንዖት ሰጥተዋል።
ዶ/ር ፈትህ ወልደሰንበት በመዝጊያ መግለጫቸው የአፍሪካን ጥቅም ማገልገል እና አህጉሪቱን በዓለም አቀፍ ደረጃ በአንድነት መወከል ክብር እና ኃላፊነት መሆኑን ተናግረዋል።
14/12/2025
የመቻል እጅ ኳስ ክለብ በተከታታይ የሲቲ ካፑን ዋንጫ አንስቷል ኦሜድላን እና ቂርቆስን በማስከተል የዋንጫ እና 100000 ሺ ብር ሽልማት እንዲሁም በዲሲፒሊን የታነፀ ክለብ ነው በማለት አዲስ አበባ ፌዴሬሽን ለመቻል የፀባይ ዋንጫ ሸልሞታል ሁለት ዋንጫ እንዲሁም ኦሜድላ 50000 3ኛ የወጣው ቂርቆስ 25000 የተዳከመው የሴቶች እጅ ኳስ ውድድርም ለመጀመሪያ ጊዜ በሲቲ ካፑ የተመለከትን ቢሆንም በኢትዮጵያ የሚወዳደሩ የሴቶች ቡድኖች እንደሌሉ ነው የሚታወቀው አ.አ ይሄንን አሳይቷል ኢትዮጵያ እጅ ኳስ ፌዴሬሽን ብዙ እንደሚጠበቅበት ይሄ ውድድር ማሳያ ነው እንዲህ እንዳለ ለሴቶች ውድድር ኮልፌ ፊናንስ ክብር ይግባው እና ሁለት ቡድን ይዞ ባይቀርብ ውድድሩ አይካሄድም ነበር አዲስ አበባ እጅ ኳስ ፌዴሬሽን ለሴቶችም የማበረታቻ የብር ሽልማት የብር መጠኑን መረጃው ባይኖረንም ለ3ቱ ቡድኖች ሸልሟል ስለዚህ እሸት ፊናንስ 1 እና ፊናንስ 2 ከ1--3 አጠናቀዋል
13/12/2025
እሁድ ትንሿ ሜዳ አይቀርም የአዲስ አበባ ሲቲ ካፕ ውድድር የፍፃሜ ጨዋታ በሴቶችም በወንዶችም
08/12/2025
የኢትዮጵያ እጅ ኳስ ፌደሬሸን 10ኛ ዓመት ፕሪሚየር ሊግ ውድድሩን ለመጀመር የእጣ ማውጣት መርሃ ግብር አከናወነ፤
ሕዳር 28፣ 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ
የኢትዮጵያ እጅ ኳስ ፌደሬሸን 10ኛ ዓመት ፕሪሚየር ሊግ ውድድሩን ለመጀመር የእጣ ማውጣት መርሃ ግብሩን የፌዴሬሸኑ አመራሮችና የውድድሩ ተሳታፊ ክለብ ተወካዮች በተገኙበት ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ አከናውኗል።
በዕጣ ማውጣት መርሀ -ግብሩ የተገኙት የፌዴሬሸኑ አመራሮች ስለ ውድድሩ አጠቃላይ ዓላማ፣ እየተከናወኑ ሰላሉ ስራዎችና በሁለት ዙር ውድድሩ ስለሚካሄድባቸው ከተሞች ከክለብ ተወካዮች ጋር ተወያይተው የዓመቱን የፕሪሚየር ሊግ ውድድር በ3 ከተሞች ለማከናወን ውሳኔ ላይ ደርሰዋል።
11 ክለቦች የሚሳተፉበት የኢትዮጲያ እጅ ኳስ ፌድሬሸን የፕሪሚየር ሊግ ውድድር በተመረጡ ሶስት ከተሞች በሁለት ዙር ተከፍሎ ከታህሳስ እስከ ግንቦት የሚካሄድ ሲሆን የመጀመሪዎቹ አራት ሳምንታት ውድድር ከታህሳስ 18/2018ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄድ ይሆናል።
ባለፉት አመታት እንደ ፌዴሬሸን በዘርፍ ውጤታማ ስፖርተኞችን ለማፍራት የስልጠና እድሎችን በማመቻቸት፣ በአፍሪካ ደረጃ የሚካሄዱ ውድድሮችን በኢትዮጲያ እንዲካሄዱ በማድረግና ለእጅ ኳስ ስፖርተኞች የስራ እድል በመፍጠር ውጤታማ ተግባራት ሲከናወን እንደቆየ በመግለፅ በዚህ ዓመት የሚካሄደው 10ኛው የእጅ ኳስ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊ ክለቦች ሀገር ወክለው በአፍሪካ መድረክ የሚሳተፉበት እድል እንደሚያገኙ ፌዴሬሽኑ ገልጿል።
የአዲስ አበባ ሲቲ ካፕ ነገ ጠዋት 3 ሰዓት ላይ ይጀምራል በትንሿ ሜዳ
19/11/2025
ለአገራችን ክለቦች ደረጃቹን የሚመጥን የምስራቅ አፍሪካ የክለቦች ውድድር
15/10/2025
ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዞን-5 የእጅ ኳስ ውድድርን እንድታዘጋጅ ተመረጠች
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5/ 2018 ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዞን-5 የእጅ ኳስ ውድድርን እንድታዘጋጅ ተመርጣለች፡፡
በውድድሩ 10 ሀገራት የሚካፈሉ ሲሆን በሁለት የእድሜ እርከን ተከፍለው ውድድራቸውን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡
በዓለም እጅ ኳስ ፌደሬሽን የሚዘጋጀው ውድድሩ ከመጋቢት 28 እስከ ሚያዚያ 2/2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ከ18 እና 20 ዓመት በታች አህጉራዊ የእጅ ኳስ ሻምፒዮና ማዘጋጀቷ ይታወሳል፡፡
ከ18 አመት ዕድሜ ዋንጫ እና ከ 20 አመት ዕድሜ 3ኛ መውጣታችን ይታወሳል ውጤቱም እጅግ በጣም ጥሩ የሚባል ነበር
13/10/2025
እንደሚታወቀው ኮልፌ በእጅ ኳስ Talent Area እንደመሆኑ መጠን ለአገራችን እጅ ኳስ ከፍተኛ አስተዋፅዎ ካደረጉት ውስጥ ነው በእጅ ኳሱ የተተኪዎች እጥረት በሚታይበት ሰዓት በአንድ አካባቢ ይሄ ሁሉ ተተኪዎች መኖራቸው አስደሳች እና ይበል የሚያሰኝ ነው ይህ ለእስፖርቱ ጥሩ መነሳሳት ነው በየክልሉ የምትገኙ አሰልጣኞችም በዚህ ልክ ስሩ ባይባልም በመጠኑ ስፖርቱ እንዳለ ኮልፌዎች እንዳሳዩት ሁላ በየአካባቢያቹ እንቅስቃሴው ካለ በውስጥ በቪድዮ በፎቶ ላኩልን የማበረታታት ስራ እንስራ
12/10/2025
መቀለ 70 እንደርታ የአፍሪካ የክለቦች የእጅኳስ ውድድሩ ዛሬ 2ኛ ጨዋታ አከናውኗል
በአፍሪካ የክለቦች እጅኳስ ውድድር ኢትዮጵያን በብቸኝነት የሚወክለው መቀለ 70 እንደርታ
በሞሮኮ ካዛብላንካ በሚከናወነው የአፍሪካ እጅኳስ ወድድር ላይ መቀለ 70 እንደርታ አምስት ክለቦች በያዘው ምድብ አንድ ላይ ተደልድሏል።
የመጀመሪያውን ጨዋታውን ከግብፁ አል አህሊ ጋር መጫወቱ ይታወቃል
2ኛው ጨዋታ በሩዋንዳው ፖሊስ ተሸንፎዋል
Click here to claim your Sponsored Listing.