Ethio Electric SC ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ

Ethio Electric SC ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ

Share

ይህ የመብራት ሃይል ስፖርት ክለብ ደጋፊዎች ፔጅ ነዉ።

29/05/2026

የጨወታ ቀን
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ኢትዮ ኤሌክትሪክ

አርባ ሁለት ነጥቦችን በመሰብሰብ አስራ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡት ንግድ ባንኮች ደረጃቸውን ለማሻሻል ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ጋር ይፋለማሉ። በመጨረሻዎቹ ስድስት ጨዋታዎች ሁለት አሸንፎ በሁለት ሽንፈት እና በሁለት አቻ የተለያየው ቡድኑ በተለይም ከተከታታይ ነጥብ መጣል በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን በማሸነፍ ዳግም ወደ አሸናፊነት ተመልሶ የነበረ ቢሆንም በቀጣይ ጨዋታ በመድን ተሽንፏል። 32ኛው ሳምንት ላይ እንዲሁ ሸገር ከተማን በማሸነፍ ወደ ድል መመለስ የቻለ ቢሆንም ባሳለፍነው ጨዋታ ሳምንት ከሀድያ ሆሳዕና ጋር ነጥብ ስለተጋራ አስተማማኝ ደረጃ ላይ ባለመቀመጡ የዛሬውን ጨዋታ ለማሸነፍ ወደ ሜዳ መግባት ይኖርበታል።

አርባ ስድስት ነጥቦችን ሰብስበው አምስተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡት ኢትዮ ኤሌክትሪኮች ወደ መሪዎች ይበልጥ ለመጠጋት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ይገጥማል። ቡድኑ በመጨረሻዎቹ ጨዋታዎች አንድ ጨዋታ ብቻ ያሸነፈ ሲሆን ተደጋጋሚ ሽንፈቶችንም በማስተናገድ ሳይጠበቅ ከዋንጫ ፉክክር እየወጣ ይገኛል። ፋሲል ከነማን 3ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፎ ወደ አሸናፊነት ተመልሶ የነበረው ቡድኑ በወልዋሎ ተሸንፎ የአሸናፊነት መንፈሱን ያጣ ሲሆን በ33ኛው ጨዋታ ሳምንት ከድሬዳዋ ከተማ ጋርም ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል። ግብ ማስቆጠር የተሳነው ቡድኑ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ መቆየት የሚፈልግ ከሆነ የፊት መስመሩን አጠናክሮ የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፍ ግድ ይለዋል። ሆኖም ግን ተጋጣሚው ያለበት ደረጃም አስጊ ከመሆኑ አንፃር ጨዋታው ጠንካራ እንደሚሆን ይጠበቃል።

ቡድኖች በሊጉ ደረጃ 17 ጊዜ ተገናኝተው ኢትዮጵያ ንግድ ባንከሰ 4 ጨዋታወችን ሲያሸንፍ ኢትዮ ኤሌክትሪክ 5 ጨዋታ ማሸነፍ ሲችል ስምንት ጊዜ አቻ ተለያይተዋል። በግንኙነታቸው 39 ግቦች የተቆጠሩ ሲሆን ባንክ 20 ግቦችን ኤሌክትሪክ ደግሞ 19 ግቦችን መረብ ላይ አሳርፈዋል።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚያጣው ተጫዋች የለም። ኢትዮ ኤሌክትሪክም በተመሳሳይ በጉዳት ሆነ በቅጣት ነፃ ሆኖ የዛሬውን ጨዋታ ያደርጋል።

21/04/2026

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ከ28ኛው ሳምንት በኃላ የደረጃ ሰንጠረዥ

21/04/2026

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ28ኛ ሳምንት አጠቃላይ ዉጤት

20/04/2026

ተጠናቀቀ
ኢትዮ. ኤሌክትሪክ 1-1 አትዮጵያ መድን

67' በዛብህ መለዮ

20/04/2026

ጎልልልልልል

ኢትዮ. ኤሌክትሪክ 1-0 ኢትዮ. መድን

67' በዛብህ መለዮ

20/04/2026

አሰላለፍ ኢትዮ. ኤሌክትሪክ ከኢትዮ. መድን

20/04/2026

ኢትዮ. ኤሌክትሪክ ከኢትዮ. መድን

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንት

በ10:00 ሰአት

ሁለቱ ቡድኖች 29 ጊዜ ተገናኝተው ኤሌክትሪክ 16 ጨዋታ በማሸነፍ ቀዳሚ ሲሆን ኢትዮጵያ መድን 8 ጨዋታዎችን አሸንፏል። በቀሪዎቹ 5 ጨዋታዎች ደግሞ አቻ ተለያይተዋል። ለወትሮውም በጎል የታጀበ የእርስ በርስ ግንኙነት ታሪክ ያላቸው ሁለቱ ቡድኖች ባደረጓቸው ጨዋታዎች 2 ጊዜ ብቻ ያለ ጎል ሲያጠናቅቁ ኤሌክትሪክ 43 ፣ መድን 28 ጎሎችን አስቆጥረዋል።

20/04/2026

Big shout out to my newest top fans! Belew Kebede, Hamza Bekele, Get Achew, Amare As Bekele, Naty Black N Whiet, NAzareth ZEleke, Amanuel Abraham

Photos from Ethio Electric SC ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ's post 17/04/2026

የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከ29ኛ እስከ 38ኛ ሳምንት ውድድር መርሃ ግብር ይፋ ሆነ፥

የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከኢትዮጵያ ዋንጫ መልስ ሚያዝያ 21/2018 ዓ.ም ይጀምራል። በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ስታዲየም እና በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚደረጉትን ከ29ኛ እስከ 38ኛ ሳምንት ያሉትን የአስር ሳምንት(ቀሪ የሊጉ ሙሉ ፕሮግራም) መርሃ ግብር ይፋ ሆኗል።

33ኛ እና 34ኛ ሳምንት የሊጉ መርሃ ግብር የኢትዮጵያ ዋንጫን ታሳቢ በማድረግ ሊሻሻል ይችላል። እንዲሁም የ37ኛ እና 38ኛ ሳምንት መርሃ ግብርም የክለቦችን ውጤት መሰረት በማድረግ ሊሻሻል ይችላል።

15/04/2026

አዳማ ከተማ ከ ኢትዮ ኤሌክትሪክ. 0-1

በተለያየ ወቅታዊ አቋም የሚገኙ ቡድኖች ያገናኘው የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ በመጀመሪያው አጋማሽ ጥቂት የግብ ሙከራዎች የተደረገበት እና ኤሌክትሪኮች የተሻለ ብልጫ የወሰዱበት ነበር።
በአጋማሹ ወደ ግብ የቀረበ ሙከራ ባያደርጉም ከተጋጣሚያቸው የተሻለ የኳስ ቁጥጥር በመያዝ ዕድሎች የፈጠሩት ኤሌክትሪኮች 43ኛው ደቂቃ ላይ
መሪ የሆኑበትን ግብ አስቆጥረዋል። ያሬድ የማነ እና በዛብህ መለዮ በቀኝ መስመር በኩል በጥሩ መንገድ ከተቀባበሉ በኋላ ያሬድ የማነ ወደ ግብነት የቀየረው ኳስም ቡድኑን መሪ ማድረግ ችሏል።

ኤሌክትሪኮች ከግቡ መቆጠር በኋላም አሸናፊ ጥሩነህ ከሳጥን ውጭ አክርሮ መቶት ግብ ጠባቂው በመለሰው ኳስ እና ሐሰን ሁሴን የተመለሰውን ኳስ ከመምታቱ በፊት ተከላካዮች ተረባርበው ባወጡት አጋጣሚ መሪነታቸው ለማስፋት ተቃርበው ነበር።

ጥሩ ፉክክር እና በርካታ የግብ ዕድሎች የተፈጠሩበት ሁለተኛው አጋማሽ በሁለቱም በኩል ለግብ የቀረቡ ሙከራዎች የተደረገበት ነበር።
አቡበከር ሳኒ እና ከቀኝ መስመር የተሻገረለትን ኳስ ተጠቅሞ በግምባር ያደረገው ሙከራ በአዳማ ከተማ በኩል በረከት ወልደ ዮሐንስ ከግራ መስመር የተሻማችውን ኳስ በግምባሩ ገጭቷት ለጥቂት ወደ ውጭ የወጣችው ድንቅ ሙከራም በኢትዮ ኤሌክትሪክ በኩል የተደረጉ የአጋማሹ ቀዳሚ ሙከራዎች ናቸው።

ከተጠቀሱ አጋጣሚዎች በኋላ አቤል ሀብታሙ በድንቅ ሁኔታ ከመሀል ሜዳ ወደ ሳጥን ገፍቶ በመግባት መቷት አግዳሚው የመለሳት ኳስ የኤሌክትሪክን መሪነት ከፍ ለማድረግ የተቃረበች ሙከራ ስትሆን ከደቂቃዎች በኋላም ሳሙኤል ዮሐንስ አሻምቷት ግብ ጠባቂው ከመለሳት በኋላ ማይክል ኪፕሩቪ ወደ ግብ መቷት እስማኢል ናሂማና ከግቡ መስመር የመለሳት ወርቃማ አጋጣሚ አዳማ ከተማን አቻ ለማድረግ ተቃርባ ነበር።

እዮብ ገብረማሪያም በጨዋታው መገባደጃ ላይ አብነት ተስፋዬ በግሩም የመልሶ ማጥቃት ሂደት አግኝቶ ያመቻቸለትን ኳስ በመምታት ያልተጠቀመባት አጋጣሚም የጨዋታው የመጨረሻ የግብ ሙከራ ስትሆን ጨዋታውም በኢትዮ ኤሌክትሪክ 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቋል።

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Website

Address

Addis Ababa