05/09/2026
4ኛው ሚሻላ ካፕ
የሙሉ ሰዓት ውጤት
ሀላባ ሸገር 4 - 2 ኤም ፋሚሊ
ሀላባ ኢንተርናሽናል ስታዲየም
Develope on
05/09/2026
4ኛው ሚሻላ ካፕ
የሙሉ ሰዓት ውጤት
ሀላባ ሸገር 4 - 2 ኤም ፋሚሊ
ሀላባ ኢንተርናሽናል ስታዲየም
05/09/2026
ሀላባ ሸገር በሚሻላ ከፕ ጨዋታ ለፍጻሜ መድረሱን አረጋገጠ።
በዛሬው ዕለት በሸገር እና በኢም ፋሚሊ መካከል በተካሄደው ጨዋታ የሀላባ ሸገር ኢም ፋሚሊን በመሸነፍ ለፍጻሜ ጨዋታ መድረሱን አረጋግጧል።
ጨዋታውን ሀላባ ሸገር 4 - 2 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
ይህንን ተከትሎ የሀላባ ሸገር ከቀይ ዛላ ጋር ለዋንጫ የሚፋለሙ ይሆናል።
05/09/2026
ቀይ ዛላ ለሚሻላ ፍጻሜ ጨዋታ ማለፉን አረጋገጠ
በሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት እየተካሄደ ባለው በክረምት ሚሻላ ከፕ ጨዋታ የቀይ ዛላ ከዋንጃ ጋር ባደረጉት ጨዋታ ቀይ ዛላ በፔናልቲ በማሸነፍ ለፍጻሜ ማለፉን አረጋገጠ
03/09/2026
ጀግኒት መልካም እድል
መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም በሚካሄደው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በዕጩ ፕሬዝዳንታዊ ተወዳዳሪ አቶ ኢሳያስ ጅራ የቀረቡ እጩ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት እና ተጠባባቂ አባላትን ስም ይፋ የተደረገ ሲሆን በዚህም የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እግር ኳስ ፕረዚዳንት ክብርት ወ/ሮ ሰርካለም ሳሙኤል ተካተዋል
ወ/ሮ ከስር መሠረቱ በስፖርት ተኮትኩተው ያደጉ፣ በዝንባሌ ብቻ ሳይሆን ሳይንሱንም በጥልቀት የተረዱ፣ “ያለኝ ዕውቀት ይበቃኛል!” ሳይሉ በስፖርት ሳይንስ Specialized በማድረግ በዘርፉ ተጨማሪ አጫጭር የወሰዱትን ስልጠና ሳይጨመር በቀለም ትምህርታቸው እስከ Masters ያጠኑ ጀግኒት እንስት እንደሆኑ አይዘነጋም ። ይኚህን የሀገር ፀጋ ሥራ አስፈፃሚ ማድረግ ከጊዜ ወደጊዜ እያንሰራራ ባለው ስፖርታችን ላይ እሴት እንደነጨመር ነውና ዕድሉን ቢያገኙ የበሳል አመራሯን ዕውቀት እንደምንቋደስ አንተራጠርም።
መልካም እድል ወ/ሮ ሰርካለም ሳሙኤል
03/09/2026
የአቶ ኢሳያስ ጂራ አዲሱ የኢትዮዽያ እግር ኳስ ፌድሬሽን ስራ አስፈፃሚ እጩ አባላት
1, አቶ አንበሴ አበበ የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌድሬሽን ፕሬዝዳንት
2, ወ/ሮ ሰርካለም ሳሙኤል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እግር ኳስ ፌድሬሽን ፕሬዝዳንት
3, አቶ አበባው ሰለሞን ባለሀብት የቀድሞው የወልቂጤ ከተማ ክለብ ፕሬዝዳንት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ተወካይ
4, አቶ ደመላሽ ይትባረክ (ማሙሽ) የቀድሞ የደቡብ ክልል የአሁኑ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እግር ኳስ ፌድሬሽን ፕሬዝዳንት
5, ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ሀላፊ እና የአሁኗ የፌድሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ አባል
6, ዶ/ር ዳኛቸው ነገሩ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ መምህር እና የአሁኑ የኢትዮዽያ እግር ኳስ ፌድሬሽን ም/ፕሬዝዳንት
7, ዶ/ር ወገኔ ዋልተንጉስ የኮተቤ ዩኒቨርሲቲ መምህር የፕሪምየር ሊጉ የውድድር እና ስነ ስርአት ሰብሳቢ
8, ኮሚሽነር አለሙ ወገራ የድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽነር እና የድሬዳዋ እግር ኳስ ፌድሬሽን ፕሬዝዳንት
ይህንን ጉዳይ ከሰማው ከሁለት ወር በፊት ነበር 🙄
03/09/2026
💛🖤 መልካም ዕድል ውልዋል ዓ/ዪንቨርሲቲ💛🖤
ሀገራችንን በአህጉራዊ የውድድር መድረክ የሚወክለው ክለባችን ሀላባ ከተማ መልካም ምኞቱን ይገልፃል ወልዋሎ ዓ/ዩ መልካም ዕድል ።
🤝 ወልዋሎ
ሀላባ ከተማ በሀላባ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ጠንካራ ልምምዱን እያደረገ ይገኛል💪
03/09/2026
መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም በሚካሄደው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኘሬዝዳንታዊ ምርጫ በዕጩ ፕሬዝዳንታዊ ተወዳዳሪ አቶ ኢሳያስ ጅራ የቀረቡ እጩ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት እና ተጠባባቂ አባላት የስም ዝርዝር
03/09/2026
ሀላባ ከተማ የነባር ተጫዋቾች ውል አራዝሟል።
ሀላባ ከተማ በ2019 የውድድር ዘመን ቅድመ ዝግጅት የጀመረ ሲሆን በዛሬው እለት የነባር ተጫዋቾች ውል አራዝሟል።
#አ/ከሪም ከሊፋ
#ቢኒያም ደግነት
#ኢዘዲን ማርሲጃ ውል ያራዘሙ ተጫዋቾች ናቸው።