Hagere ሀገሬ

Hagere ሀገሬ

Share

"እውነተኛው የትምህርት ዓላማ አዋቂነት እና መልካም ባህሪ ነው"

24/05/2025

"ጃዋር መሃመድ እና የቤተ መንግስት ሽያጭ"

መቼስ የጃዋር መሃመድ ቀልድና የጥፋት ሱስ ማለቂያ የለውም፤ "አዲሱ ቤተመንግስት ተሸጦ ለሀኪሞች ደሞዝና ጥቅማጥቅም ይከፈል" ማለቱ ቀልድ እንደማያልቅበት ያሳያል፤ በየማህበራዊ ሚዲያው "ሀኪሞች ታሰሩ፣ ስራ አቆሙ፣ አደሙ፣ ተሳደዱ፣ ተራቡ፣ ተቸገሩ . . .በሽተኞች ተጉላሉ፣ ህክምና አጡ፣ ሞቱ . . . " የሚለው ደግሞ የጥፋት ሱስ እንዳለበት አመላካች ነው። ሲደማመር የለመደው አመጽ፣ መገዳደል፣ ማቃጠል፣ ማፈናቀል . . . .የማስቀጠል አባዜ እንደተጠናወተው አረጋጋጭ ነው።

ለመሆኑ 'እሺ ይሸጥ' እንኳ ቢባል ቤተ መንግስት ዶሮ ነው እንዴ? የጓሮ አትክልት ነው?🤔 ብድግ ተደርጎ በአቅራቢያ በሚገኝ ገበያ የሚሸጥ ነው❓

ወይስ እንደቆራሌው በየአደባባዩ ወጥተን
"አዲስ ቤተ መንግስት የሚገዛ!
አለ አዲስ ቤተ መንግስት!
ሽያጭ - ሽያጭ! አለ የቤተመንግስት ሽያጭ!
አዲስ ያልተኖረበት . . . ❗"እንበል❓

" ሽያጭ❗ ያልተኖረበት❗
ንጉሥ ያልተቀመጠበት❗
ከከተማ ወጣ ያለ፣ ንጹህ አየር ያለበት❗
መሰረተ ልማት የተሟላለት ቤት መንግስት አለ❗ . . . " እያልን እንዙር❓



ይሸጥ ቢባል እንኳን ከሰነድ ማዘጋጀት እስከ ገዢ ማግኘት ምን ያህል ጊዜ ሊወስድ ይችላል❓
ታዲያ ከመንግስት ጋር ለመወያየትና ለመደራደር እንኳን ፍቃደኛ ላልሆኑ #በጃዋሪያን የአመፅ ፖለቲካ ለተጠለፉ ጥቂት አድመኛ ሀኪሞች እንዴት መፍትሄ ሊሆን ይችላል❓ ወይስ መንግስት ቤተ መንግስት ለመሸጥ ከተስማማ ወደ ሥራ ይመለሳሉ❓
ድንቄም የፖለቲካ ሳይንቲስት🤔😬

ነገሩ፣ ቤተ መንግስት መሸጥ ቀላል እንዳልሆነ ሁሉ፣ የሀኪሞችን ደሞዝ መክፈልም ቀላል አይደለም።

መፍትሄው ቀላል ነው። ሀኪሞች “ሱሪ በአንገት ነው፣ ዛሬ ካልተከፈለን ነገ አንኖርም! ህመምተኞች ከሞቱም ድፍት ይበሉ . . .” ከመሳሰሉ ኢሰብአዊ አስተሳሰብ ይላቀቁ። እነ ጃዋር ከበከሏቸው የፖለቲካ ቫይረስ ይላቀቁ፤ ወደስራም ይመለሱ። ከሁሉም ክልሎች ወኪሎቻቸውን ይላኩ። (ከዚህ በፊትም ተወካይ ላኩ ተብሎ እንደነበር መረጃ አለኝ)
ከመንግስት ጋር ሻይ ቡና እየጠጡ ጥያቄዎቻቸውን ያቅርቡ፣ ይወያዩ፣ ይመካከሩ፣ በጋራ መፍትሄ ያፍልቁ። ቤተ እምነትም ቤተ መንግስትም ሳይሸጥ የሚገባቸውን ያግኙ። (ባይሆን መንግስት በተስማሙት መሰረት መክፈል ካልቻለ ስለሽያጩ ማንሳት ይቻላል)😁



እውነት ለመናገር ቤተ መንግስት እየታነፀ ለመሆኑ አገርም አለምም ያውቃል። ለመጪው ትውልድ የሚተላለፍ፣ የሀገር ምልክት የሚሆን፣ የታሪክ ሀብትን የሚያጎለበት፣ የኢትዮጵያ ልዕልናን የሚገልጽ . . . ታላቅ ቤተ መንግስት እየተገነባ ለመሆኑ ህዝብም ያውቃል። በመሆኑም ማንም ብድግ ብሎ እንደጓሮ አትክልት፣ እንደ ቤት እንስሳት፣ እንደ ሱቅ ሸቀጣ ሸቀጥ . . . የሚሸጠው አይደለም። ወይም እንደ የግል ጌጣጌጥ ሲቸግር ለግብይት የሚያቀርበው አይደለም። በእውነቱ የዚህ አስተሳሰብ ተጠቂ የሆነ ሰው ነገ ሥልጣን ሲያገኝ ኢኮኖሚያዊ ችግር ቢገጥመው የአገር ደህንነትና ዘላቂ ጥቅም ቁልፍ የሆኑ ተቋማት እና መሬትን ሸጦ ሲጨርስ አገርም ከነህዝቡ ከመሸጥ አይመለስም። ይህ ጃዋር ያረጋገጠልን ሊያደርገው የሚችል እውነት ነው።



በመሰረቱ የፖለቲካ ሳይንስ በነጭ ተምሬያለሁ ከሚል ቆዳ አምላኪ የሚጠበቀው የቤተ መንግስት ሽያጭ ሀሳብ አልነበረም። የጤና ሥርዓቱ የሚሻሻልበት፣ የጤና ባለሙያዎች በድካማቸው ልክ ክፍያ የሚያገኙበት፣ በጀት ድልድል ለጤናው ዘርፍ ትኩረት የሚሰጥበት . . . የፖሊሲ ሀሳብ ማፍለቅ ነበር የሚጠበቅበት።

Photos 20/06/2022

# ፍትህ_ለንፁሃን !!
የኢትዮጵያን ስም ደጋግሞ በማንሳት ብቻ ጥሩ ኢትዮጵያ መሆን
አይቻልም!!
ህዝቧ እንዳይገደል፣እንዳይራብ፣እንዳይፈናቀል የሚያስፈልገው ስራ
እንጂ በስሟ ሲምሉ እና ሲገዝቱ መዋል ብቻ አይደለም!!
ኢትዮጵያ ልጄ ብላ የምታመሰግነው የሰራላትን እንጂ ያወራላትን
አይደለም!!!

07/06/2022

ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከገባችበት ችግር እንድትወጣና
ሰላሟ እንዲመለስ የመፍትሄ ሀሳብ የማያቀርብ የፖለቲካ ፓርቲ (ወይም
የፓርቲዎች ጥምረት) እና አክቲቪስት/ግለሰብ የለም፤ መንግስትም
እንዲሁ ከችግር እንወጣበታለን ያለውን መንገድ ተከትሎ እየሰራ ነው፡፡
እነዚህን ‹ለሀገር እንሰራለን› የሚሉ ግለሰቦች፣ ፓርቲዎችና መንግስትን
እንዳይግባቡ የሚያደርጋቸው ዋናው ምክንያት የቆሙበት ቦታና የመሸጉበት
ጽንፍ ነው፡፡
በዚያ በኩል፣. . .
አንድ ግለሰብ ወይም ፓርቲ ስለሀገሩ ለመነጋገር/ለመስራት ሲነሳ ግቡ
ሀገሩና ዜጋው ብቻ መሆን አለበት፡፡ ስልጣንና ገንዘብ ከሀገሩና ከወገኑ
እንኳን ሊወዳደር ሚዛን ላይም መቅረብ የለበትም፡፡
ምእራባውያኑ የገቡባቸው ሀገራት (ኢራቅ፣ ሊቢያ፣ የመን፣ አፍጋኒስታን፣
ሱማሌ) የገጠማቸውን የተመለከተ፣ ምእራባውያኑ በኢትዮጵያ ላይ እንዴት
ያለ አሉታዊ ፍላጎት እየታወቀ ‹የውጭ ሀይል ኢትዮጵያ ይግባ› ብሎ
የሚነሳ፣ አራት አመት ጠብቆ በመጪው ምርጫ ከመወዳደር ይልቅ ‹ዛሬ
መንግስት ተለውጦ የሽግግር መንግስት ካልተመሰረተ ሀገር ይፈርሳል›
ወዘተ. እያለ ጉባኤ እየጠራ መግለጫ የሚያወጣ የፓርቲ ድርጅትም ሆነ
አክቲቪሰት/ግለሰብ ሀገሩ ላይ ቆሞ፣ ሀገሩን አስቀድሞ የተነሳ ነው
ለማለት አይቻልም፡፡
በዚህ በኩል፣ . . .
ከላይ ከተጠቀስኳቸው በተለየ ሀገራቸውንና ወገናቸውን ብቻ ስቀድመው
ለችግሮች መፍትሄ የሚያቀርቡ አክቲቪስቶች/ግለሰቦችና ፓርቲዎች
(ወይም የፓርቲ ጥምረቶች) ባይበዙም አሉ፤ መንግስት የእነዚህን አካላት
የመፍትሄ ሀሳብ ሊያዳምጥና ተግባራዊ ሊያደርግ ይገባል፡፡
መንግስትነት የሀገር አስተዳዳሪነትን እንጂ ለሀገር ተቆርቋሪነትን
አያጎናጽፍም፡፡ ደርግ በሀገር ፍቅር የተለከፈ፣ ወያኔ/ኢህአዴግ የሀገር
ፍቅርን የተጸየፈ መንግስታት ነበሩ፤ ስለሀገር ተቆርቋሪነታቸው ሰማይና
ምድር ቢሆንም ሁለቱም ሀገር አስተዳዳሪዎች ነበሩ፡፡
በመሆኑም ሀገር የሚያስተዳድር መንግስት ምንጊዜም ከእሱ እኩል ወይም
በበለጠ ለሀገራቸው የሚያስቡ ግለሰቦችና ፓርቲዎች እንዳሉ በመገንዘብ
በሩን መክፈት፣ ለሀገራቸው እንዲሰሩ እድል መስጠት አለበት፡፡
በዚህና በዚያ በኩል . . . .
እንኳን የሀገርን የቤተሰብም ችግር ለመፍታት መነጋገር ያስፈልጋል፤
ተቀራርቦ መነጋገር፡፡ የየራስን ጥግ ይዞ በየተራ መናገር መነጋገር
አይደለም፡፡ ስለኢትዮጵያ ያገባናል የሚሉ በየተራ መናገር አቁመው
መነጋገር አለባቸው፤ በርግጥ ጉዳያቸው ሀገርና ህዝብ ከሆነ፡፡
ሁለቱም ወገኖች በየጽንፉ ከገነቡት የራስ ሀሳብ ጣኦትን ማምለኪያ ታዛ
ወጥተው ወደ መሀል መምጣት አለባቸው፡፡ የገዛ ሀሳባቸውን ቋሚና ማገር
አድርገው በየጽንፉ ከገነቡት ዋሻ ወጥተው መሀል ላይ መገናኘት/መነጋገር
መጀመር አለባቸው፡፡
ተራርቀው ከቆሙበት ወደ መሀል መጥተው መነጋገርና ሀገርንና ህዝብን
ከችግር እንዲላቀቅ መስራት አለባቸው፡፡ ለግማሽ ምእተአመት ኢሊቶቹ
ያራመዱት ጽንፍ - ረገጥ ፖለቲካ ህዝብ ላይ ያደረሰው ሰቆቃ፣ ሀገርን
የከተተበት አዘቅት ሊያማቸው ይገባል፡፡
ሀገርም ይበቃታል! ህዝቡም ይበቃዋል፡፡

04/06/2022

This is a time to work together.

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Arba Minch'?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

Address

Arba Minch'