MØFË SPØRT

MØFË SPØRT

Share

Life is loading........

05/04/2022

አርቴታ ይቅርታ ጠይቋል

የአርሰናሉ አሰልጣኝ ሚካኤል አርቴታ ቡድኑ ትላንት ምሽት ከሜዳው ውጭ ወደ ስልሀረስት ፓርክ አቅንቶ በፕሪሚየር ሊጉ በቀድሞ አማካዩ ፓትሪክ ቪዬራ በሚሰለጥነው ክሪስታል ፓላስ ሶስት ለዜሮ መሸነፉን ተከትሎ ደጋፊዎቹን ይቅርታ ጠይቋል።

ስብስብ ወቀሳ እና ትችቶችን ለመቀበልም ዝግጁ መሆን ያለበት ጊዜ ነው ሲል ተናግሯል።ሽንፈቱን ተከትሎ መድፈኞቹ አንድ ተስተካካይ የጨዋታ መርሀ ግብር እየቀራቸው ከከተማ ተቀናቃኛቸው ቶትንሀም ሆትስፐር በጎል ክፍያ አንሰው አምስተኛ ስፍራ ላይ ለመቀመጥ ተገደዋል።

አርሰናል ከፓላስ ጋር በሊጉ ካደረጋቸው የመጨረሻ ስምንት ጨዋታዎች መካከል በአንዱ ብቻ ድል ማድረግ የቻለ ሲሆን በአምስቱ ነጥብ ሲጥል በሁለቱ ሽንፈት ለማስተናገድ ተገዷል።

ንስሮቹ በበኩላቸው በሁሉም ውድድሮች ባደረጓቸው የመጨረሻ ሁለት ጨዋታዎች ሰባት ጎሎችን ተጋጣሚያቸው መረብ ላይ ማሳረፍ የቻሉ ሲሆን ምንም ጎል ሳያስተናግዱም መውጣት ችለዋል።

sport

05/04/2022

ሩኒ ዩናይትድ ከውጤት ቀውሱ እንዲወጣ ማውሪሲዪ ፖቸቲኖ መሾም አለበት አለ

የቀድሞ የማንቺስተር ዩናይትድ አጥቂ እና የአሁኑ የደርቢ ካውንቲ አሰልጣኝ ዌይን ሩኒ የኦልድትራፎርዱ ክለብ ከገባበት ውጤት ቀውስ ወጥቶ በድጋሚ ከአመታት በፊት ወደ ነበረው ጥንካሬ ለመመለስ አርጀንቲናዊውን የፓሪስ ሴንት ዠርመን አሰልጣኝ ማውሪሲዪ ፖቸቲኖ መሾም እንዳለበት አስታወቀ።

የ36 አመቱ ሩኒ ጨምሮ ቀያይ ሰይጣናቱ በቀጣይ የውድድር ዘመን በሻምፒየንስ ሊጉ የመሳተፍ እድል ይኖራቸዋል የሚል እምነት እንደሌለው ተናግሯል።

ዩናይትድ ባሳለፍነው ቅዳሜ በሜዳው ኦልድትራፎርድ የብሬንዳን ሮጀርስን ሌይስተር ሲቲ አስተናግዶ አንድ አቻ መለያየቱን ተከትሎ የቶፕ ፎሩን ቦታ የማግኘት እድሉ አጣብቂኝ ውስጥ ለመግባት መገደዱ ይታወሳል።

በሌላ በኩል ፈረንሳዊው ኢንተርናሽናል የአለም ዋንጫ አሸናፊ አማካይ ፖል ፖግባ ክለቡን መልቀቅ እንዳለበት ሩኒ አሳስቧል።

የ29 አመቱ ተጫዋች በኦልድትራፎርድ ያለው የኮንትራት ውል ቆይታ በውድድር ዘመኑ መጨረሻ የሚጠናቀቅ መሆኑ ይታወቃል።

እስካሁን ድረስም ውሉን የማደስ ምንም አይነት ፍላጎት አላሳየም።
sport

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Awassa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Telephone

Website

Address

Sport News
Awassa
HAWASSA