Mudu Baba Butajira official

Mudu Baba Butajira official

Share

ጠቅላላ እውቀት

25/08/2025

የጨዋታው ውጤት፡ ኒውካስል 2 – 3 ሊቨርፑል 🔥
በሴንት ጀምስ ፓርክ (St. James’ Park) ላይ የተከናወነው ጨዋታ እውነት አስደናቂ ነበር!

ሊቨርፑል በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት መርሐግብር ከኒውካስል ጋር ያደረገውን ጨዋታ በድራማዊ ሁኔታ 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፎ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል።

የሊቨርፑል የማሸነፊያ ጎሎችን ግራቨንበርች፣ ሁጎ ኤኪቲኬ እና የ16 አመቱ ወጣት ሪዮ ንጉሞሀ ሲያስቆጥሩ፣ ለኒውካስል ደግሞ ብሩኖ ጉማሬሽ እና ዊሊያም ኦሱላ ጎል አስቆጣሪዎች ነበሩ።

በተለይ የጨዋታውን ውጤት የወሰነው የ16 አመቱ ተጨዋች ሪዮ ንጉሞሀ በ100ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ ያሳረፋት ድንቅ ጎል ናት።

በዚህ ድል ሊቨርፑል የሊጉን የመጀመሪያ ሁለት ጨዋታዎች በድል በማጠናቀቅ ስድስት ነጥቦችን ማግኘት ችሏል።

የቀጣይ ጨዋታዎች መርሐግብር፡
* እሁድ: ሊቨርፑል ከ አርሰናል
* ቅዳሜ: ሊድስ ዩናይትድ ከ ኒውካስል ዩናይትድ

እያያችሁ ነበር ግን ?

What a game

⚽️🧐

🌴🌴🌴Mudu Baba Butajira official

25/08/2025

🗣ፍሎሪያን ዊርትዝ በፕሪሚየር ሊግ እና በቡንደስሊጋ መካከል ባሉ ልዩነቶች ላይ ሲናገር:-

“ሙሉ ለሙሉ የተለየ የእግር ኳስ አይነት አይደለም፣ ልክ እንደ ሌላ ጨዋታ ነው። ይሁን እንጂ፣ በአካል ጥንካሬው የጠነከረ እና ምናልባትም ትንሽ ተጨማሪ ሩጫ የሚያስፈልገው ነው። ተቃዋሚዎች በሙሉ ጊዜው ይበልጥ ተጠግተው ይጫወታሉ። ነገር ግን ከቡንደስሊጋው ለምጄዋለሁ፣ እዚያም ብዙ ጊዜ በልዩ ጥበቃ ስር ነበርኩ።"

𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚| baba butalira official

21/08/2025

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አራተኛው መጽሐፍ - “የመደመር መንግሥት” የያዘቸው ቁምነገሮች
********************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የመደመር መንግሥት” የተሰኘው አራተኛ መጽሐፋቸውን በተመለከተ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት በዘመናዊት ኢትዮጵያ ያሉት መንግሥታት የመንግሥታቸውን ቅርፅ፣ እሳቤ እና አደራረግ ሰንደው አስቀምጠው አያውቁም።

ምናልባትም በአፍሪካ ደረጃም በእንደዚህ ዓይነት መልክ መንግሥታቸው ያለው እሳቤ፣ የአተገባበር ሥልቱን፣ የሚከውንበትን መንገድ፣ ሊያሳካ የሚያስበውን ግብ እና ውጤት በዝርዝር ያስቀመጠ፣ ለሕዝቡም የገለጠ መንግሥት የለም።

እናም ይህ በራሱ “የመደመር መንግሥት” የተሰኘውን ሰነድ ፈር ቀዳጅ ያደርገዋል።

የመደመር መንግሥት ዋና ሐሳቡ ግን በፅንስ (በንድፍ) እና በፍልስፍና ያየነውን፣ ታሪኩን ጉዞውን ያወቅነውን፣ ትውልድ እንዴት እንደሚሠራ ያስቀመጠው መደመር ተቋማዊ ቅርፅ እንዲይዝ ማድረጉ ነው።

መደመር መንግሥታዊ ቅርፅ እንዲይዝ የሚያደርገው ይህ ሰነድ እንደሆነ እና ከግል እና ከቡድን ወጥቶ እንደመንግሥት እሳቤው እንዴት እንደሚሠራ በዝርዝር እንደሚያስቀምጥም ገልጸዋል።

በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የሚታየው አንደኛው ጉዳይ “እኛ እና የተቀረው ዓለም የተላለፍነው የት ነው?” ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ስብራቶቻችን የት ጀመሩ? የሚለውን እና ያንን ከዓለም የለየንን ጉዳይ በዝርዝር ማንሣቱ ነው።

ሁለተኛው ጉዳይ ደግሞ ኋላ ለመቅረታችን ምክንያት የሆኑ ፈተናዎች፣ ተግዳሮቶች ምንድን ናቸው? የሚለውን በዝርዝር ማተቱ ነው።

በተጨማሪም፤ በእኛ እና በዓለም መካከል የተፈጠረውን ክፍተት፤ እንዴት ልናጠብበው እንችላለን? ምን ዓይነት መደመራዊ አካሄድ ብንከተል ክፍተቱ ሊጠብብ እንደሚችል ደግሞ ይተነትናል።

ታሪኩን ካነሣ እና ክፍተቱን ካየ በኋላም፤ ክፍተቶቹ መጥበብ የሚችሉባቸው መንገዶችንም ያመላክታል።

ያንን ለማድረግም ከተለመደው የመክዳት አካሄድ ተላቅቀን መደመራዊ ፈጠራ፣ ፍጥነት እና የዝላይ መንገዶችን መከተል እንዳለብን ይመክራል።

ካልፈጠርን፣ ካልፈጠንን በአንዳንዱ ጉዳዮች ደግሞ ካልዘለልን በስተቀር ያንን ልዩነት እያጠበብን መሄድ ያቅተናል ብሎ በዝርዝር ያትታል - የመንደመር መንግሥት መጽሐፍ።

ሐሳቡን ሲዘረዝርም ከቀደሙት መንግሥታት ኀልዮት ጋር ራሱን ያወዳድራል። ለምሳሌ ገበያ መር ካልንበት ጊዜ ጋር ራሱን ያወዳድራል፤ ወይም የእዝ ኢኮኖሚ ባልንባቸው ወቅቶች የነበረውን አሠራር እና አደራረግ ያወዳድራል።

እንዲሁም ልማታዊ መንግሥት ያልባቸው ጊዜያትም እነዚያን ኀልዮቶችን እንዳለ አይቷቸው፤ አንሥቶ በንፅፅር ለምን ይህኛውን እሳቤ እንደምንከተል ያመላክታል።

መደመርን ፍልስፍናዬ አድርጌ ነው ብልጽግናን የማረጋግጠው የሚል መንግሥት ምን ዓይነት ባህሪያት እንዳሉት በዝርዝር ያስቀምጣል።

ስለሚከተለው ስትራቴጂ፤ ስለሚያስመዘግበው ውጤትም፤ በተጨማሪም በሀገር ውስጥም፣ ከሀገር ውጭም ስለሚኖረው ግንኙነት በዝርዝር ያትታል።

በዚህ ሂደት ውስጥ የተሻገረ፣ የተለወጠ እና የዘመነ ገጠር እንዴት መፍጠር እንደምንችል በዝርዝር እንደሚያትትም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያብራሩት።

ዘመናዊ እና የተሳለጠ ከተማ እንዴት መፍጠር እንደምንችል፤ በኢንዱስትሪው፣ በቱሪዝሙ ያሉን ውጤቶች በፈጠነ መንገድ አሰናስሎ ለሀገር ጥቅም እና ዕድገት እንዴት ማዋል እንደሚቻል የመደመር መንግሥት በዝርዝር ያስቀምጣል።

ይህንን ሰነድ በደንብ ጊዜ ወስዶ ያየ ሰው መንግሥት ምን ዓይነት መልክ፣ ፍላጎት፣ አደራረግ እንዳለው ያ

21/08/2025
18/08/2025

“ ትልቅ ውጤት ነው በቡድኔ ኮርቻለሁ“

“ ቪክቶር ዮኬሬሽ ጥሩ ሲሰራ ነበር “

የውድድር አመቱን በድል የጀመሩት መድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ በተመዘገበው ውጤት መደሰታቸውን ተናገረዋል።

ሁለት ጥሩ ነገሮችን ማድረጋቸውን በጨዋታው የገለፁት ሚኬል አርቴታ “ የተቆጠረው ጎል እና ስህተቶችን መቆጣጠራቸው “ መሆኑን ገልፀዋል።

“ ትልቅ ውጤት ነው “ ሲሉ ድሉን የገለፁት አሰልጣኙ “ በቡድኔ ኮርቻለሁ ነገር ግን ማሻሻል የሚገቡን ነገሮች አሉ “ብለዋል።

ስለ አዲሱ ፈራሚያቸው ቪክቶር ዮኬሬሽ ሲናገሩም “ ብዙ ጥሩ ነገሮች ሲሰራ ነበር “ ሲሉ ተናግረዋል።

“ ወደ ኦልድ ትራፎርድ ሄዶ የመጀመሪያ የሊግ ጨዋታን ማሸነፍ ትልቅ ጅማሮ ነው “ ሚኬል አርቴታ

Baba Butajira official

15/08/2025

እስኪ ስለ ጓደኛችሁ ንገሩኝ እኔ ስለ እናንተ ባህሪ ልንገራችሁ
ጓደኛችሁ ምን አይነት ነው ?

Mudu Baba Butajira official

15/08/2025

የኤሎን መስክ ልጅ ነኝ ያለው የኬንያዊው የይገባኛል ጥያቄ ውድቅ ሆነ

በማህበራዊ ሚዲያ ብዙዎችን አነጋግሮ የነበረው፣ ኬንያዊው ኒያኩንዲ ኪቢሩ የቢሊየነሩ ኤሎን መስክ የበኩር ልጅ ነኝ ያለው የይገባኛል ጥያቄ፣ በማስረጃ እጥረት እና በጊዜ ቅደም ተከተል መዛባት ምክንያት ውድቅ መደረጉ ተዘግቧል።

የይገባኛል ጥያቄው ምን ነበር?

የ40 ዓመቱ ኪቢሩ እናቱ በ1980ዎቹ መጀመሪያ ላይ በማሳይ ማራ ሆቴል ከመስክ ጋር ግንኙነት እንደነበራት ተናግሯል። የፈለገውም የገንዘብ ጥቅም ሳይሆን እውቅና ብቻ እንደሆነ ገልጿል። አንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችም በሁለቱ ሰዎች መካከል የአካል መመሳሰል እንዳለ ተናግረው ነበር።

ለምን ውድቅ ሆነ?

ይህ የይገባኛል ጥያቄ በዋናነት በሁለት ምክንያቶች ውድቅ ተደርጓል፦

* የጊዜ ቅደም ተከተል መዛባት: ኤሎን መስክ የተወለደው በ1971 ሲሆን፣ ኪቢሩ በተፀነሰበት ወቅት ማለትም በ1980ዎቹ መጀመሪያ ላይ፣ መስክ ገና ከ12 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ውስጥ ነበር። ይህ ደግሞ ሰውየው የተናገረውን ታሪክ ከእውነታ የራቀ ያደርገዋል።

* የማስረጃ እጥረት: መስክ በዛን ጊዜ ኬንያን እንደጎበኘ የሚያሳይ ምንም አይነት የተረጋገጠ ማስረጃ የለም።

ኪቢሩ የዲኤንኤ ምርመራ እንዲደረግለት ያቀረበው ጥያቄም እስካሁን ምላሽ አላገኘም። በመሆኑም፣ ይህ የይገባኛል ጥያቄ ተአማኒነት የሌለው እና በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት ያላገኘ መሆኑ ተጠቁሟል።

Via መናኽሪያ

🧐🧐🧐

🌴🌴🌴Mudu Baba Yayatu Lj

14/08/2025

"ቼልሲ ከቻምፒየንስ ሊግ የምድብ ማጣሪያ ያልፋል ብዬ አላስብም ።"

🗣|| ጄሚ ካራገር

(via WeAreTheOverlap)

Mudu Baba Butajira official

14/08/2025

ጊዜ ሰጠኝ ብለህ በሰው ግፍ አትስራ,
ዓለም ሁለት ፊት ናት ይደርስሀል ተራ! 😌

14/08/2025

👏😮

ቸልሲ የክለቦች የዓለም ዋንጫ የሽልማት ገንዘብ ለዲዮጎ ጆታ እና ለአንድሬ ሲልቫ ቤተሰቦች ሊሰጥ ነው!

ሰማያዊዎቹ በቅርቡ በተካሄደው የክለቦች የዓለም ዋንጫ ውድድር ላይ ለተሳተፉ ተጫዋቾቻቸው ለመስጠት የታቀደውን 15.5 ሚሊዮን ዶላር (11.4 ሚሊዮን ፓውንድ) ጉርሻ፣ በክለቡና በተጫዋቾች የጋራ ስምምነት መሰረት፣ በቅርቡ ህይወታቸው ያለፈው የዲዮጎ ጆታ እና የአንድሬ ሲልቫ ቤተሰቦች ጋር ሊያካፍሉ መሆኑ ተዘግቧል።

ይህ የቸልሲ ውሳኔ የክለቡን ሰብአዊነት እና
የቡድን መንፈስ የሚያሳይ ታላቅ ተግባር ነው!

ቸልሲ 👏👏👏

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴Mudu Baba Butajira official

10/08/2025

👔 Managers to win most UCL titles:
🏆 Carlo Ancelotti – 5
🥈 Zidane, Guardiola, Paisley – 3

🔝 The elite of European football!
Mudu Baba Yayatu Lj

08/08/2025

በከምባታ ባህላዊ ልብስ እና በርኔጣ (ቆሜ) ተውባው ከምባታ የቱሪስት መስህቦችን ይጎብኙ፥

Mudu Baba Butajira official

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Riyadh?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Website

Address

Riyadh