15/11/2022
እውነታ ስፖርት
ትሪቡን ስፖርት
ስፖርትን ለመከታተል ትክክለኛው ቦታ
═════════════
➮የተለያዩ ስፖርታዊ ታሪኮች
15/11/2022
10/11/2022
የአርሰናል_የድል_ምልክት አርሴን_ቬንገር_በኮከቦች_ገፅ
ON YOU TUBE EWNETA SPORT
10/11/2022
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ለፍፃሜ ጨዋታ ሳያልፍ ቀረ
በሱዳን አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው ከ20 ዓመት በታች የሴካፋ ዞን ሻምፒዮና እና የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ውድድር የሆነው ይህ ሻምፒዮና ላይ፣ ተካፋይ የነበረው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በደቡብ ሱዳን ተሸንፎ ለዋንጫ ጨዋታ ሳያልፍ
ቀርቷል::
በመጀመሪያ ጨዋታው ከታንዛኒያ ጋር 2ለ2 ተለያይቶ በሁለተኛው ዩጋንዳን 1ለ0 አሸንፎ ነበር ::
ከደቡብ ሱዳን ጋር ለነበረው ጨዋታ ያለፈው፣ በዚህ ጨዋታውም በመደበኛው ደቂቃ 2ለ2 ተለያይቶ፣ በመለያ ምት 4ለ2 በሆነ ውጤት በደቡብ ሱዳን ተሸንፏል::
በአሰልጣኝ ዕድሉ ደረጄ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በዚህ ጨዋታ አሸንፎ ቢሆን ኖሮ ለዋንጫ ከማለፉ ጎን ለጎን በግብፅ ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳታፊ መሆኑን ያረጋግጥ ነበር::
ይህ ሳይሳካለት የቀረው ቡድኑ የደረጃ ጨዋታውን ከአስተናጋጅ ሀገሯ ሱዳን ጋር ይጫወታል።
08/11/2022
የእንግሊዙ ታላቅ ክለብ ሊቨርፑል ለሽያጭ ሊቀርብ ነው
ሊቨርፑልን በባለቤትነት የሚያስተዳድሩት የፌንዌይ ስፖርት ግሩፕ ክለቡን ለመሸጥ ዝግጁ መሆናቸውን ዘ አትሌቲክ አስነብቧል።
በፈረንጆች የጊዜ አቆጣጠር 2010 ጥቅምት ወር ላይ ከቀድሞ ባለቤቶቹ ጆርጅ ጂሌት እና ቶም ሂክስ ላይ በ300 ሚሊዮን ፓውንድ የገዙትን ክለብ አሁን ከ12 አመታት የባለቤትነት ቆይታ በኋላ ለመሸጥ የተዘጋጁት ፌን ዌይ ስፖርትስ ግሩፕ "ትክክለኛውን ደንብ
እና ግዴታን ተከትሎ የሚቀርቡ ጥያቄዎችን ለማጤን ዝግጁ ነን" ብለዋል::
አክለውም ባለቤቶቹ "ለሊቨርፑል ቀጣይ ስኬት ግን ቁርጠኛ ሆነን እንቀጥላለን" ሲሉ ተናግረዋል::
ተቋሙ ክለቡን በባለቤትነት ከጠቀለለ በኋላ በጀርመናዊው አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ እየተመራ ታላላቅ የድል ታሪኮችን አስመዝግቧል።
ከ30 አመታት ቆይታ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ዋንጫን ከማንሳታቸው ባለፈ የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ፣ የኤፍ ኤ ካፕ እና የሊግ ካፕ ዋንጫን አሳክተዋል።
ከዋንጫዎቹ ባለፈ የክለቡ ባለቤቶች ለሊቨርፑል ባላቸው ጥሩ የተቆርቋሪነት ስሜት ይታወቃሉ።
የስታዲየም እድሳት፣ የአዲስ ልምምድ ማእከል ስራ፣ ጠንካራ የቡድን ግምባታ እና ሌሎችም የሚጠቀሱ አወንታዊ ስራዎችን አከናውነዋል።
በቅርቡ እስከ 3 ቢሊዮን ፓውንድ የሚጠጋ የግዢ ዋጋ ለሊቨርፑል ቀርቦላቸው ውድቅ ያደረጉት ባለቤቶቹ በምን ያህል ዋጋ ክለቡን ሊሸጡ ይችላሉ የሚለው ተጠባቂ ጉዳይ ሆኗል።
ሐዋርያው ጴጥሮስ እንደፃፈው
08/11/2022
በጥሎ ማለፉ የአምና የፍጻሜ ተፋላሚዎቹ ማድሪድና ሊቨርፑል መገናኘታቸው ከወዲሁ ቀልብ ሳቢ ሆኗል፡፡ የፈረንሳዩ ክለብ ፓሪሰን ዠርማ ከ ጀርመኑ ባየር ሙኒክ ሌላኛው ትልቅ ፍልሚያ ይሆናል፡፡
የዘንድሮው የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ በቱርክ ኢስታንቡል አታቱርክ ኦሊምፒክ ስታዲየም ይደረጋል፡፡
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Contact the business
Website
Address
Adama
0000