17/12/2023
መድፈኞቹ የሊጉን መሪነት ተረክበዋል !
በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ አስራ ሰባተኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል ከብራይተን ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉን መሪነት በጊዜያዊነት መረከብ ችለዋል።
የአርሰናልን የማሸነፊያ ግቦች ጋብሬል ጄሱስ እና ካይ ሀቨርትዝ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።
በሌሎች ጨዋታዎች አስቶንቪላ ብሬንትፎርድን 2 ለ 1 እንዲሁም ዌስትሀም ዩናይትድ ዎልቭስን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
የዌስትሀም ዩናይትድ ጃርድ ቦውን በዘንድሮው የውድድር ዘመን አስራ አንደኛ የፕርሚየር ሊግ ግቡን አስቆጥሯል።