15/04/2026
Congratulations to and on your well-deserved promotion to the CBE Ethiopia Premier League!
We, at Garo Gere Sports Management, are truly delighted by your remarkable achievement. Your hard work, dedication, and perseverance have paid off, and you have earned your place among the top clubs in the Higher league of Ethiopian football.
We wish you the very best of luck and great success as you compete at the highest level. May your journey in the CBE Ethiopia Premier League be filled with outstanding performances, growth, and continued accomplishments.
👏👏👏 & I have a big clap for both of you!!👏👏👏
ለጋሞ ጨንቻ እግር ኳስ ክለብ እና ለሀላባ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ወደ CBE የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በማደጋቹ እንኳን ደስ አላችሁ!
እኛ በጋሮ ገሬ ስፖርትስ ማኔጅመንት በዚህ ታላቅ ስኬታችሁ እጅግ ደስ ብሎናል። ያሳያችሁት ትጋት፣ ጽናት እና ቁርጠኝነት ውጤት አመጥቶአል።
በCBE የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ላይ በሚያደርጉት ጉዞ ሁሉ መልካም ዕድል እና ታላቅ ስኬት እንመኛለን። ጉዞአችሁ በውጤታማ አፈጻጸም፣ በእድገት እና በተጨማሪ ስኬቶች ይሞላ ዘንድ እንመኛለን።
Photo Credit #ዳጉ #ስፖርት
14/03/2026
Happy Fiche Chambaalalla - Sidama New Year! 🎉
Wishing peace, happiness, and success to the Sidama people.
May this new year bring victory and a trophy to the Sidama clubs leading the CBE Ethiopian Premier League
Gere, FIFA Licensed Football Players Agent ⚽
09/01/2026
Garo Gere Sports Management is now on the InScout Network ⚽🌍
Players and coaches come and work with us, grow your profile on social media, and connect yourself with European football opportunities. Let’s build your future together!
27/09/2025
በካፍ ቻምፒየንስ ሊግ ሀገራችንን የወከለው ኢትዮጵያ መድን አዲስ አበባ ላይ ከሳምንት በፊት የዛንዚባሩን ሞላንግዴን 2ለ0 ማሸነፍ የሚታወስ ሲሆን በዛሬው ዕለት ደግሞ ከሜዳው ውጪ የመልስ ጨዋታውን አድርጎ 3ለ2 መሸነፍ ቢችሉም በድምር ውጤት ግን 4ለ3 በማሸነፍ ወደ ሁለተኛው ዙር ማለፋቸውን በማረጋገጣቸው የጋሮ ገሬ ስፖርትስ ማኔጅመንት ተቋም ለክለቡ አባላት በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት ይወዳል !
16/07/2025
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ የፊፋ የእግር ኳስ ኤጀንቶች ማኅበር እየታዩ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት እና በቀጣይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውይይት አደረጉ፡፡
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዝደንት አቶ ኢሳያስ ጅራ፣ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ባህሩ ጥላሁን፣ የቲኤም ኤስ ባለሙያ ወ/ሮ ዘውድነሽ ይርዳው፣ የኢትዮጵያ የፊፋ የእግር ኳስ ኤጀንቶች ማህበር ፐሬዝደንት አቶ ኤዶሚያስ በቀለ፣ የማህበሩ ም/ፐሬዝደንት አቶ በረከት ደረጀ፣ የማህበሩ የውጭ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ኢዩኤል ደባሽ፣ የማህበሩ የሒሳብ ሹም አቶ ገሮ ገረመው እና የማህበሩ ህዝብ ግንኙነት አቶ ኤርሚያስ በቀለ በተደረገው ውይይት ህገወጥነትን ስለመከላከል፣ ሰለ ሀገራዊ የእግር ኳስ ኤጀንቶች መተዳደሪያ ደንብ፣ ታዳጊዎችን ስለማብቃት፣ ስለ ፕሮፌሽናልነት፣ የሀገራችንን ተጫዋቾች በማብቃት ወደ ውጭ ሀገራት ስለመላክ፣ ክለቦችን ስለማብቃትና ማሳደግ ዙርያ ሀሳቦች ተነስተው የተወያዩ ሲሆን በቅርበት ለመሥራትና የደረሱበትን ለመገምገም ቀጣይ ቀጠሮ በመያዝ ተጠናቋል።
02/07/2025
ዓሊ ሱለይማን አሁንም የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ነው 👌
የ2017 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በመድን የበላይነት ከቀናት በፊት ሰኔ 18 ዕለተ ሐሙስ መጠናቀቁ ይታወሳል በመዝጊያውም ዕለት የተለያዩ የሽልማት ስነ ስርአቶች የተካሄዱ ሲሆን የሀዋሳ ከተማውም አጥቂ ዓሊ ሱለይማን በቡድን ጓደኛው በረከት ሳሙኤል ውክልና በ21 ጎሎች የሊጉ ከፍተኛ ጎል አግቢ ሆኖ በመቋጨቱ የገንዘብ እና የዋንጫ ሽልማት እንደተበረከተለትም ይታወሳል።
ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን በትላንት ዕለት ሦስት ክለቦች የፋይናንስ ህግን ጥሰዋል በሚል ቅጣት ያስተላለፈ ሲሆን ሀዋሳ ከተማም ቅጣት የተጣለበትን አጥቂው እስራኤል እሸቱን ቅጣት ተጥሎበት እያለ በፍርድ ቤት ውሳኔ ከህግ አግባብ ውጪ አሰልፎ በመገኘቱ ተጫዋቹ በአራት ጨዋታዎች ላይ ተሳትፎ ስለነበረው ሀዋሳ ከተማ ተጫዋቹ በተሰለፈባቸው ጨዋታዎች ሁሉ የተከናወኑ ጨዋታዎች ሙሉ ተሰርዘው ሀዋሳ ከነበረው ነጥብ ላይ አስራ ሁለት ነጥብ እና አስራ ሁለት ጎሎች እንዲቀነስበት ተወስኗል።
ይህንንም ተከትሎ የተለያዩ አካላት አመቱን በከፍተኛ ጎል አግቢነት በ21 ጎሎች ፈፅሟ ኮከብ የተባለው ዓሊ ሱለይማን የጎል አስቆጣሪነቱ ይነጠቃል በሚል የተሳሳቱ መረጃዎች እያሰራጩ ይገኛል ፣ ነገር ግን ሀዋሳ ከተማ ከአርባምንጭ ከተማ ፥ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ፥ ከድሬዳዋ ከተማ እና ፋሲል ከነማ ጋር ያደረጋቸው ጨዋታዎች ላይ እስራኤል በመሰለፉ ነጥቦች እና ጎሎች ከላይ እንደተጠቀሰው የተሰረዘበት ሲሆን ከአራቱ ጨዋታዎች ደግሞ ዓሊ በፋሲሉ እና በጊዮርጊሱ ጨዋታ ላይ ሁለት ጎሎችን ብቻ ያስቆጠረ በመሆኑ አጥቂው ካገባው 21 ጎሎች ሁለት ጎሎች ብቻ ተቀንሶበት አሁንም በ19 ጎሎች የከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ሆኖ ያጠናቀቀው ራሱ ዓሊ መሆኑን ለማስገንዘብ እንወዳለን።