Kelemu Balageru

Kelemu Balageru

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Kelemu Balageru, Sport & recreation, Addis Ababa.

Sports entertainment is a type of spectacle which presents an ostensibly competitive event using a high level of theatrical flourish and extravagant presentation, with the purpose of entertaining an a

01/09/2022

እባካችሁ የትግራይ እናቶችና አባቶች ጩኹ፣ አልቅሱ!

በስማም! የህወሃት ምሽጎች ሲሰባበሩ ያለቁ የህወሃት ታጣቂ ፎቶግራፎች በብዛት ደርሰውኝ ተመለከትኳቸው እውነት ለመናገር ሰው ሆኖ መፈጠርን ያስጠላል።
ለማይጨበጠው ቅዠታቸው ሲባል ይህን ሁሉ ወጣት ማስጨረስ ምን አይነት እብደት ነው? አይ ህወሃት! እባካችሁ የትግራይ እናቶችና አባቶች ጩኹ፣ አልቅሱ!
ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም

01/09/2022

ሁሉም ነገር ከእምዬ ኢትዮጵያ በታች ነው!!!
ዝም ብለህ ግፋ!
ወደፊት ብቻ!!!

ነሐሴ፳፮ ቀን፳፻፲፬ዓ/ም
💪💪💪💪💪

01/09/2022

የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት ወደ ትግራይ ገብቶ ሁሉን ሲቆጣጠር ህዝቡ መብራት ስልክና የባንክ አገልግሎት ያለከልካይ እርዳታን ጨምሮ ያገኛል።
💪💪💪💪
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹 ድል ለኢትዮጵያ!

01/09/2022

ወ*ኔ የአማራን ህዝብ ከምድረ ገፅ ለመፋቅ በፈፀመው አሰቃቂ ጥቃት የተፈጠረው ጠባሳ ጠገግ ሳይል "የአማራ ልጅ ፋኖ ወዳጄ ልቤ ነው" ካለ በፍርሃት ርዷል፥ ፈርቷል ተንበቅብቋል ማለት ነው‼️

04/05/2022

ጤነኛን መመረዝ የሞተን ሰው ማከም፤
ወዳጅን አጣልቶ ለማስታረቅ መድከም፤
ከበግ መሀል ቆሞ የቀበሮ ጸሎት፤
በእጅ አዙሪት ገድለዉ የአዞ እንባ ቢያነቡት፤
ማንም ከእዉነት ቢሸሽ ባድር ባይ ሆዱ፤
ይዘገያል እንጂ መቼ ይቀራል ፍርዱ!።
እናት ዶሮን ገድሎ ጭልፊት አባራሪ ፤
አባት ገደል ገፍቶ የሙት ልጆች ጧሪ፤
የማስመሰል ኑሮ የሞት መንገድ ይብቃን፤
ክፋትን ሞከርነዉ መልካም ነገር ይዉጣን።
ህሊና ደሳለኝ

💪ከምርጥ ጽሑፎች

29/04/2022

⛪አትንኳት ጎጆዬን እንዲሁም ዘማለች፤
⛪ ትልቁን አዳራሽ ይዛዉ ትወድቃለች፤

ስልጤ ዞን የሳንኩራ ንቡ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያ ተቃጥላለች!!

19/03/2022

በዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ላይ እርማት እንዲደረግ የአማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም ጠየቀ።

የአማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም በዛሬው እለት ለትምህርት ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ የ12ኛ ክፍል መግቢያ ፈተና እና ውጤት ላይ እርማት እንዲደረግ ጠይቋል።

የመግቢያ ፈተናውን ውጤት ተከትሎ የሚወጡት መረጃዎች ያልተለመዱና አስደንጋጭ ናቸው ያለው የአማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም በተወሰኑ ተማሪዎችና ወላጆች ግፊትና ጫና የተስተካከሉ ውጤቶች ለተፈጠረው ስህተት ሁነኛ ማሳያዎች ናቸው ብሏል።

የአማራ ትምህርት ቢሮ የሁሉንም ትምህርት ቤቶች ውጤት ዝርዝር መረጃ በመሰብሰብ ለትምህርት ሚኒስቴርና ለሕዝብ ይፋ ማድረግ እንደሚገባው የጠቆመው ፎረሙ ትምህርት ሚኒስቴርና የፈተናዎች ድርጅት ለችግሩ ትኩረት ሰጥተው ለማረም እድል ያገኛሉ ብሎ እንደሚያምን በደብዳቤው ገልጿል።

በተማሪዎችና ወላጆች እየቀረበ ያለውን ጥያቄ ሁሉም ወገን በቅንነት ተቀብሎ የድጋሜ እርማትን እንዲሁም ተጨማሪ ማጣራት ማድረግ በዜጎች ዘንድ ፍትሐዊነትና ተአማኒነት ከማረጋገጡም በላይ ለአገር ሰላምና መረጋጋት ይጠቅማል ሲልም ፎረሙ አሳስቧል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ፈተናውና ውጤቱ ላይ እየተነሱ ያሉ ጥያቄዎች እንደ ፖለቲካ ጥያቄ አቻችሎና ሰምቶ በመተው የሚፈቱ ሳይሆን የትውልዱን እድል የሚወስኑ በመሆናቸው በፍጹም አካዳሚያዊ ስነ ምግባርና ከፍተኛ መሆን አለበት ብሏል ፎረሙ።

ፎረሙ በጻፈው ደብዳቤም ሁሉም አካላት ችግሩ መፍትሔ እንዲያገኝ ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጠይቋል።

ፈተና በደቦ እየተሠራ መልካም ትውልዶችን መፍጠር አይቻልም ያለው ተቋሙ ጉዳዩ ከብሔር አውድ ፍፁም ነጻ እንዲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነት እንዲሠሩ ጠይቋል።

ተማሪዎችና ወላጆች ጥያቄው መልስ እስኪያገኝ ተረጋግተው እንዲጠብቁም ጥሪ አቅርቧል።

አማራ ኮሚዩኒኬሽን

11/07/2021

#ሀምሌ 5 2008 ዓ.ም ሲታወስ የአማራ ህዝብ የፓለቲካ ንቃተሂሊና የተበሰርበት ቀን ነዉ ።
እንኳን አደርሳችሁ!!
ድል ለወልቃይት ሰቲት ሁመራ💪💪

15/06/2021

👱‍♀ :- ቢራ ትጠጣለህ??🤔

👱‍♂ :- አዎ🙄

👱‍♀ :- በቀን ምን ያህል ትጠጣለህ😳

👱‍♂ :- ሶስት ብቻ🙄

👱‍♀ :- አንድ ቢራ ስንት ነው...🤔

👱‍♂ :- 15birr🤔

👱‍♀ :- ለስንት አመት ጠጥተሀል🤔

👱‍♂ :- ለ 20 አመት🤔

👱‍♀ :- አየህ እስከዛሬ ብቻ 324,000 ብር አውጥተሀል !! ያንን ገንዘብ ቆጥበህ ቢሆን ከነወለዱ አውሮፕላን ትገዛ ነበር🤷‍♀!!!

👱‍♂ :- አንቺ ትጠጫለሽ🤔?

👱‍♀ :- ኧረ በፍፁም 🙄

👱‍♂ :- የታል አውሮፕላንሽ😳🤔😁😂

12/06/2021

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሚማሩ የ 3ኛ አመት የሳይኮሎጂ ተመራቂ ጓደኛሞች ነገ Final ፈተና እያላቸዉ ማታ ሲጨፍሩ አመሹ ፡፡ እናም ወደ ተከራዩበት ቤት ሲመለሱ ለማጥናት ጊዜ ስላልነበራቸዉ ወዲያዉ ተኝተዉ ጠዋት በመነሳት ወደ መፈተኛ ክፍሉ ይሯሯጣሉ ፡፡

በዚህ ጊዜ ሳያጠና መፈተኑ የጨነቀዉ አንድ ተማሪ አሪፍ ሀሳብ ያቀርባል ፡፡
"ለምን ግን ሳናጠና ከምንፈተን ፥ አስተማሪያችንን ትናንት ማታ ወደ ግቢ ላይብረሪ ስንመጣ የምንመጣበት ታክሲ ጎማ ፈንድቶ እሱ እስኪስተካከል ጠበቅን ከዛም ደግሞ በመንገድ ላይ አንዱ ጓደኛችን ታሞ እሱን ሆስፒታል ወሰድን ግቢ እንደገባንም ስለደከመን ሳናጠና አደርን አንለዉም " የሚል ሃሳብ አቀረበ ፡፡ በዚህ ጊዜ ሁለቱም በሀሳቡ በደስታ ተስማምተዉ ለአስተማሪዉ ሊነግሩት ወደ ቢሮዉ በፍጥነት አመሩ ፡፡ የሳይኮሎጂዉ ፕሮፌሰርም ባጋጠማቸዉ ነገር እጅግ በጣም አዝኖ ለነሱ ብቻ ሌላ ፈተና አዉጥቶ በነጋታዉ ሊፈትናቸዉ ተስማሙ ፡፡

3ቱ ጓደኞችም በብልጠታቸዉ እጅግ በጣም ተደስተዉ ቀጥታ ወደ ኬኔዴ ላይብረሪ ገብተዉ ማጥናት ጀመሩ ፡፡ በዛን ቀን ደግሞም ማታዉን ጨምረዉ ወጥረዉ ሲያጠኑ ካማሹ በኅላ በነጋታዉ ለፈተና ቀረቡ ፡፡ አስተማሪዉም ሌላ አንድ ፈታኝ አስተማሪ ጨምሮ 3ቱን ተመራቂ ተማሪዎች ሰፊ ክፍል ካስገባቸዉ በኀላ አራርቆ አስቀምጦ የፈተና ወረቀ ሰጣቸዉ ፡፡

3ቱም ጎደኞች ያለፈዉ ቀን እጅግ በጣም አጥንተዉ ስለነበር በተጨማሪ ትናንት ከተፈተኑት ጓደኞቻቸዉ ስለ ፈተዉ ብዙ መረጃ ይዘዉ ገብተዉ ስለነበር ፈተናዉን እንደሚሰቅሉት ያላንዳች ጥርጣሬና በሙሉ መተማመን ነበር የገቡት ፡፡

የሳይኮሎጂ ፕሮፌሰሩም የፈተና ወረቀቱን ሰጣቸዉና በሉ ስሩ ተማሪዋቼ አለ ፡፡ 3ቱም ተማሪዋች ፈተናቸዉን ገልብጠዉ ስማቸዉንና ID ቁጥራቸዉን ከፃፉ በኀላ ጥያቄዉን ማንበብ ጀመሩ ፡፡ ጥያቄዋቹ እንዲህ የሚሉ ነበሩ ?
1. የፈነዳዉ የታክሲ ጎማ የትኛዉ ነበር ?
ሀ.የፊት ቀኝ ለ.የፊት ግራ
ሐ. የኀላ ቀኝ መ.የኀላ ግራ
2.ጎማዉ የፈነዳዉ የት አካባቢና ስንት ሰአት ነዉ?___________________
3. ጎማዉ የተቀየረዉ የት ጎሚስታ ቤት ነዉ?
________________
4.የታመመዉን ጓደኛችሁን የት ሆስፒታል ወሰዳችሁት?
_______________

መልካም ፈተና ! መልካም ቅዳሜ
ይህን ፈተና ከደፈናችሁ Final exam ለመፈተን ብቁ ናችሁ !
😂
Just 😁😁😁

11/06/2021

!
🔑ራቁትክን ትወለዳለህ፤ እርቃንህን ወደ መቃብር ትወርዳለህ
🔑 በጥርስ አልባው ድድህ እየጋጥክ ትጀምራለህ፤ ጥርሱን ባረገፈው ድድህ እያልጎጠጎጥክ ትጨርሳለህ።
🔐የሕይወትን ትግል እየዳህ ትጀምራለህ፤ አጎንብሰህ ትጨርሳለህ፡፡
🌽መጀመሪያህ መጨረሻህ ነው፤የጀመርክበትን አትርሳ፤ መጨረሻህ ነውና፡፡የጀመርክበትን አትናቀው፤ ትጨርስበታለህና፡፡ ተራ ሠው ሆነህ ትጀምራለህ፤ ተምረህ ዕውቀት ብትጨምርም፤ ነግደህ ሃብት ብታገኝ፤ ተሹመህ በሕዝብ ላይ ብትሠለጥን፤
#ዘመንም ተምኔታዊ ነው፡፡
🌅መስከረም ጥቅምት ብሎ ያስጀምርህና መስከረም ብሎ ይመጣብሃል፤ ሠኞ ማክሠኞ ብለህ ተጉዘህ፤ እንደገና ሠኞ ትላለህ፡፡
እናም ሕይወት አዙሪት ናት!

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

Address


Addis Ababa