21/10/2025
💵👀 ከ16 አመት በፊት ሞሮኮ ለመሀመድ ስድስተኛ አካዳሚ ግንባታ 65 ሚሊየን ዶላር ፈሰስ አድርጋ ነበር።
በዚህ አካዳሚ ውስጥ 30 ሄክታር የሚሸፍን የእግር ኳስ ሜዳዎች፣ የቅንጦት ሆቴሎች፣ ጂም እና ትምህርት ቤቶች ሳይቀር ይገኙበታል።
ሞሮኮ ዋና አላማዋ የወደፊት ኮከቦችን ለማፍራት ነው። በዕቅዱ መሰረትም ጎዳና ላይ የሚጫወቱትን በመመልመል ወደ ተሻለ ደረጃ ማድረስ ላይ ያተኮረ ነበር።
ፕሮጀክቱ ፍሬ አፍርቷል፡-
➡ ከ20 አመት በታች ቡድነለ የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነ።
➡ ከ23 አመት በታች ቡድኑ የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነ።
➡ ከ17 አመት በታች ቡድኑ የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነ።
➡ ከ20 አመት በታች ቡድኑ የአፍሪካ ዋንጫ የፍፃሜ ተፋላሚ ሆነ።
➡ በ2024 የኦሎምፒክ ጨዋታዎች ሶስተኛ ደረጃ ላይ ይዛ አጠናቀቀች።
➡ በኳታር በ2022 የአለም ዋንጫ ለግማሽ ፍፃሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ የአፍራካ ሀገር በመሆን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቀቀች።
በታዳጊዎች ላይ ኢንቨስት ማድረግ ለወደፊት እግርኳስ ብሩህ መንገድ ነው 👏🏻
05/09/2025
ኢትዮጵያ ከ ግብፅ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ይገናኛሉ
በአፍሪካ ሀገራት የዓለም ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከግብፅ ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
ምድብ አንድ ላይ የሚገኝው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድኑ ከ7 ጊዜ የአፍሪካ ሻምፒኗ ግብፅ የሚያደርገው ጨዋታ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በካይሮ ኢንተርናሽናል ስቴዲየም ይደረጋል፡፡
ካደረጓቸው 6 የምድብ ጨዋታዎች አንዱን ብቻ ያሸነፉት ዋልያዎቹ በግብፅ በሚያደርጉት የምድቡ 7ኛ ጨዋታ ከባድ ፈተና ይጠብቃቸዋል፡፡
የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን መስራቾቹ ሁለቱ ሀገራት ባላቸው የእርስበርስ ግንኙነት ግብፅ የተሻለ የማሸነፍ ብልጫ አላት፡፡
ከአሁን በፊት በተገናኙበት 19 ጨዋታ ኢትዮጵያ ማሸነፍ የቻለችው ሦስቱን ብቻ ሲሆን ግብፅ 13 ጊዜ አሸንፋለች፡፡ በቀሪ ሦስት ጨዋታዎች ደግሞ አቻ ተለያይተዋል፡፡
ዋልያዎቹ የግብፅን ብሔራዊ ቡድን ለመጨረሻ ጊዜ ያሸነፉት ከሦስት ዓመት በፊት በማላዊ በተደረገው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ እንደነበር ይታወሳል፡፡
ከዚህ በኋላ ከግብፅ ባደረጓቸው ሁለት ጨዋታች ግን በሁለቱም ተሸንፈዋል፡፡
ምሽት 4 ሰዓት ላይ ለሚደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታው በሚደረግበት ስቴዲየም የመጨረሻ ልምምዱን ሰርቷል፡፡
የየምድቡ አሸናፊዎች ብቻ በቀጥታ በዓለም ዋንጨው በሚሳተፉበት ማጣሪያ ምድብ አንድን ግብፅ በ16 ነጥብ ስትመራ ኢትዮጵያ በ6 ነጥብ 5ኛ ደረጃ ላይ ቀምጣለች፡፡
30/07/2025
ሃይላት ገ/ ግዮርጊስ 📍
በኢትዮዽያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በክብር የሚታወሰውን ሃይላት ገ/ግዮርጊስን ለመጠደገፍ የተዘጋጀ ተንቦላ ሜዳው የሚገኝ ሲሆን እንግዶቻችን በመግዛት ለወንድማችን አጋርነታችንን እናሳየው ።
ESCFE
11/07/2025
ህብስት ጥሩነህ 📍
20ኛውን ESCFE ከሚያደምቁልን ሙዚቀኞች መሃል ከልጅነት ጀምሮ በኢትዮዽያ ሙዚቃ ውስጥ እንደተወደደች መኖር የቻለችውን ህብስት ጥሩነህ አንዷ ናት ።
ከህብስት ጋር ፍራንክፈርት ላይ ጥሩ ግዜ ይኖረናል 💯
አይቀርም ❗️
ESCFE
14/03/2025
!! እሁድ ይጫወታሉ!!
ሽሮሜዳን ወክለው በአዲስ አበባ ስፖርት ለሁሉም የጤና ቡድኖች እግር ኳስ ጨዋታ የ2017ዓም ውድድር የሚወዳደሩት ካባ ሜዳና አጋጣሚ ጤና ቡድን በወንድማማቾች ደርቢ እሁድ በጉቶ ሜዳ ይገናኛሉ!!!
Vs #አጋጣሚ
🏟ቦታ ጉቶ ሜዳ
⌚️ሰዓት 6:00
በቦታው በመገኘት ቡድንዎን ይደግፋ!!
በዚህ የሽሮሜዳ ወንድማማቾች ደርቢ ጨዋታ በመገኘት እንዲታደሙ ተጋብዘዋል!!
መልካም ዕድል ለሁለቱም ቡድን!!
🙏✅⚽️🏟