Abyssinia sport/ አቢሲኒያ ስፖርት

Abyssinia sport/ አቢሲኒያ ስፖርት

Share

ከእሁድ እስከ እሁድ ፈጣን የመረጃ ምንጭ!

04/10/2025

ሰማያዊዎቹ ወሳኝ ድል አሳክተዋል !

በሳምንቱ ተጠባቂ የፕርሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ ከሊቨርፑል ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።

የቼልሲን የማሸነፊያ ግቦች ሞይሰስ ካይሴዶ እና እስቴቫኦ ሲያስቆጥሩ ለሊቨርፑል ኮዲ ጋክፖ ከመረብ አሳርፏል።

ሊቨርፑል በሁሉም ውድድሮች ሶስተኛ ተከታታይ ሽንፈቱን አስተናግዷል።

ቼልሲ ከሶስት የሊግ ጨዋታዎች ነጥብ መጣል በኋላ ወደ ድል ተመልሰዋል።

የሊቨርፑልን መሸነፍ ተከትሎ አርሰናል ሊጉን መምራት ጀምሯል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

2️⃣ ሊቨርፑል :- 15 'ነጥብ
6️⃣ ቼልሲ :- 11 ነጥብ

ቀጣይ መርሐግብር ?

ቅዳሜ - ኖቲንግሃም ከ ቼልሲ

እሁድ - ሊቨርፑል ከ ማንችስተር ዩናይትድ

Photos from Abyssinia sport/ አቢሲኒያ ስፖርት's post 04/10/2025

አርሰናል እና ዩናይትድ ድል አድርገዋል !

አርሰናል ከዌስትሀም ዩናይትድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉን መሪነት ተረክቧል።

የመድፈኞቹን የማሸነፊያ ግቦች ዴክላን ራይስ እና ቡካዩ ሳካ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።

ማንችስተር ዩናይትድ በበኩሉ ከሰንደርላንድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2ለ0 በሆነ ውጤት ረቷል።

ለቀያይ ሴጣኖቹ የማሸነፊያ ግቦችን ሜሰን ማውንት እና ቤንጃሚን ሼስኮ አስቆጥረዋል።

ቡካዩ ሳካ በፕርሚየር ሊጉ 200ኛ ጨዋታውን ሲያደርግ 100 የግብ ተሳትፎ ማድረግ ችሏል።

ዌስትሀም ዩናይትድ በውድድር ዘመኑ አምስተኛ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

1️⃣ አርሰናል :- 16 ነጥብ
6️⃣ ሰንደርላንድ :- 11 ነጥብ
8️⃣ ማንችስተር ዩናይትድ :- 10 ነጥብ
1️⃣9️⃣ ዌስትሀም ዩናይትድ :- 4 ነጥብ

ቀጣይ መርሐግብር ?

ቅዳሜ - ፉልሀም ከ አርሰናል

እሁድ - ሊቨርፑል ከ ማንችስተር ዩናይትድ

28/09/2025

መድፈኞቹ ጣፋጭ ድል ተቀዳጅተዋል !

በፕርምየር ሊግ መርሐ ግብር አርሰናል ከኒውካስል ዩናይትድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

የአርሰናልን የማሸነፊያ ግቦች ሚኬል ሜሪኖ እና ጋብሬል ማግሀሌስ በግምባር በመግጨት አስቆጥረዋል።

ለኒውካስል ዩናይትድ ኒክ ቮልተማደ ከመረብ አሳርፏል።

ሚኬል ሜሪኖ በ 2025 ከየትኛውም የአርሰናል ተጨዋች በላይ 7️⃣ የፕርሚየር ሊግ ጎሎችን አስቆጥሯል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

2️⃣ አርሰናል :- 13 ነጥብ
1️⃣5️⃣ ኒውካስል ዩናይትድ :- 6 ነጥብ

ቀጣይ መርሐግብር ?

ረቡዕ - አርሰናል ከ ኦሎምፒያኮስ ( ሻምፒየንስ ሊግ )

ረቡዕ - ዩኒየን ከ ኒውካስል ዩናይትድ ( ሻምፒየንስ ሊግ )

24/08/2025

ማንችስተር ዩናይትድ ነጥብ ተጋርቷል !

በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት መርሐግብር ማንችስተር ዩናይትድ ከፉልሀም ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቋል።

የማንችስተር ዩናይትድን ግብ ሙኒዝ በራሱ መረብ ላይ ሲያስቆጥር ስሚዝ ሮው ፉልሀምን አቻ አድርጓል።

በጨዋታው ብሩኖ ፈርናንዴዝ ያገኘውን ፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀም ቀርቷል።

ማንችስተር ዩናይትድ በሊጉ የመጀመሪያ አንድ ነጥብ ሲያገኝ ፉልሀም ሁለት ነጥቦችን ሰብስቧል።

በቀጣይ የሊጉ መርሐግብር

⏩ ቅዳሜ - ማንችስተር ዩናይትድ ከ በርንሌይ
⏩ ቅዳሜ - ቼልሲ ከ ፉልሀም

23/08/2025

አርሰናል ተከታታይ ድሉን አሳክቷል !

በፕርሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት መርሐግብር አርሰናል ከሊድስ ዩናይትድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 5ለ0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል።

የመድፈኞቹን የማሸነፊያ ግቦች ጁሪየን ቲምበር 2x ፣ ቪክቶር ዮኬሬሽ 2x እና ቡካዩ ሳካ ማስቆጠር ችለዋል።

ስዊድናዊው የፊት መስመር አጥቂ ቪክቶር ዮኬሬሽ የመጀመሪያ የፕርሚየር ሊግ ጎሉን ማስቆጠር ችሏል።

የ 15ዓመቱ ማክስ ዶውማን ከኢታን ንዋኔሪ በመቀጠል በፕርሚየር ሊግ ጨዋታ የተሳተፈ ሁለተኛው በእድሜ ትንሹ ተጨዋች ሆኗል።

አርሰናል ከ 2023/24 በኋላ ከየትኛውም ክለብ በበለጠ 33 የቆሙ ኳሶችን ከማዕዘን ምት አስቆጥረዋል።

አርሰናል የመጀመሪያ ሁለት ጨዋታዎችን በማሸነፍ ሊጉን በበላይነት በመምራት ላይ ይገኛሉ።

በቀጣይ የሊጉ መርሐግብር

⏩ እሁድ - ሊቨርፑል ከ አርሰናል
⏩ ቅዳሜ - ሊድስ ዩናይትድ ከ ኒውካስል ዩናይትድ

17/08/2025

አርሰናል አመቱን በድል ጀምሯል !

በሳምንቱ ተጠባቂ መርሐግብር አርሰናል ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

የመድፈኞቹን የማሸነፊያ ግብ ሪካርዶ ካላፊዮሪ በግምባር በመግጨት ማስቆጠር ችሏል።

መድፈኞቹ ባለፉት አራት የውድድር አመታት ከማዕዘን ምት 6️⃣5️⃣ ጎሎችን ከመረብ አሳርፈዋል።

በቀጣይ የሊጉ መርሐግብር

⏩ እሁድ - ማንችስተር ዩናይትድ ከ ፉልሀም
⏩ ቅዳሜ - አርሰናል ከ ሊድስ ዩናይትድ ጋር የሚገናኙ ይሆናል።

17/08/2025

የእረፍት ሰዓት !

በሊጉ የመጀመሪያ ሳምንት መርሐግብር አርሰናል ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር እያደረጉ የሚገኙትን ጨዋታ 1ለ0 እየመሩ ወደ መልበሻ ቤት አምርተዋል።

- የአርሰናልን የመሪነት ግብ ሪካርዶ ካላፊዮሪ አስቆጥሯል።

🟨 የቢጫ ካርድ የተመለከቱ ተጫዋቾች እነማን ናቸው ?

- በመጀመሪያው አጋማሽ በአርሰናል በኩል ሪካርዶ ካላፊዮሪ የማስጠንቀቂያ ካርድ ተመልክቷል።

⚽ የጨዋታው የኳስ ቁጥጥር ምን ይመስላል ?

- በመጀመሪያው አጋማሽ ማንችስተር ዩናይትድ 56% - 44% የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ነበራቸው

15/07/2025

ለቼልሲ የተሰጠው ዋንጫ ተመሳሳዩ መሆኑን ትራምፕ ተናገሩ

ከትላንት በስቲያ በክለቦች የዓለም ዋንጫ ድል ወቅት ቼልሲ ያነሳው ዋንጫ ቅጂው እንደነበር ተዘግቧል።

ዶናልድ ትራምፕ ከDAZN አስተናጋጅ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ለቼልሲ የተሰጠው ዋንጫ ሁለተኛው ነው ዋናው እኔ ቢሮ አስቀምጬዋለሁ ፊፋ ለዘለዓለም አስቀምጠው ውሰደው ብሎኛል ብለዋል

ትራምፕ በቀጣይ አሜሪካ ውስጥ እግርኳስ ሶከር ሳይሆን ፉትቦል ተብሎ እንዲጠራ አዝዣለሁ ሲል አሳውቀዋል

08/06/2025

ፖርቹጋል ሻምፒዮን 🏆 ሆነች !

የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን የስፔን አቻውን በመለያ ምት 5ለ3 በማሸነፍ የኔሽንስ ሊግ አሸናፊ መሆኑን አረጋግጧል።

በመደበኛው የጨዋታ ክፍለጊዜ ሁለቱ ቡድኖች ጨዋታቸውን 2ለ2 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።

የስፔንን ግብ ዙቢሜንዲ እና አኦያርዛባል ሲያስቆጥሩ ለፖርቹጋል ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና ሜንዴዝ ከመረብ አሳርፈዋል።

ፖርቹጋል ሁለተኛ የአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ዋንጫዋን ማሸነፍ ችላለች።

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን 138ኛ ግቡን ማስቆጠር ችሏል።

የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን የኔሽንስ ሊግ ዋንጫን ሁለት ጊዜ ያሳካ የመጀመሪያ ብሔራዊ ቡድን ሆኗል።

ፖርቹጋል ስፔንን በ 21ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ አሸንፋታለች።

24/05/2025

አርሰናል የሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ አሸነፈ !

የአርሰናል ሴቶች ቡድን የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታውን ከባርሴሎና ጋር አድርጎ 1ለ0 በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆነዋል።

አርሰናል በታሪኩ ለሁለተኛ ጊዜ የሴቶች የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫውን ማሸነፍ ችሏል።

የሀገር ውስጥ ሶስትዮሽ ዋንጫ አሸናፊው ባርሴሎና ከተከታታይ ሶስት አመታት የውድድሩ አሸናፊነት በኋላ ዋንጫውን አጥተዋል።

የሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ያሸነፈ ብቸኛው የእንግሊዝ ቡድን የሆነው አርሰናል ሪከርዱን በሌላ ዋንጫ አሻሽሎታል።

የአርሰናል ዋና አሰልጣኝ ሬኔ ሴሌገርስ የሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ ያሸነፈች በታሪክ የመጀመሪያዋ ኔዘርላንዳዊት አሰልጣኝ መሆን ችላለች።

21/05/2025

🏆🏆 CHAMPION 🏆🏆⚪️

በዩሮፓ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ ቶተንሀም ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1ለ0 በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆነዋል።

የቶተንሀምን ወሳኝ የማሸነፊያ ግብ ብሬናን ጆንሰን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

የለንደኑ ክለብ ቶተንሀም በታሪኩ ሶስተኛውን የዩሮፓ ሊግ ዋንጫ ማሸነፍ ችሏል።

አሰልጣኝ አንሄ ፖስቴኮግሉ ክለብ በተረከቡ ሁለተኛ አመታቸው ዋንጫ የማሸነፍ ሪከርዳቸውን አስቀጥለዋል።

ማንችስተር ዩናይትድ በሚቀጥለው የውድድር ዘመን በአውሮፓ መድረክ የማይሳተፍ ይሆናል።

17/04/2025

“ አርሰናሎች ለመከላከል ነው የመጡት “

“ ጨዋታው ከባድ ነበር “ ቫዝኩዌዝ

የሎስ ብላንኮዎቹ ተጫዋች ሉካስ ቫዝኩዌዝ ጨዋታው ባሰቡት መንገድ እንዳልነበረ ከጨዋታው በኃላ ተናግሯል።

“ ጨዋታው ከባድ ነበር “ ያለው ቫዝኩዌዝ “ ጨዋታው ከቁጥጥራችን ውጪ አልነበረም ፣ ሆኖም የምንፈልገውን ማድረግ ሳንችል ቀርተናል “ ብሏል።

ተጋጣሚያቸው አርሰናልን “ ለመከላከል ነው የመጡት በመጀመሪያው አጋማሽ ምንም አላደረጉም “ ሲል የገለፀው ቫዝኩዌዝ “ በሁለተኛው አጋማሽ የሚያሸንፉበትን አጋጣሚዎች አግኝተዋል “ ሲል ተደምጧል።

ለሽንፈቱ የቡድኑ አባላት ሀላፊነት መውሰድ እንደሚገባቸው የገለፀው ቫዝኩዌዝ “ ማድሪዳዊያን ያለንን ሁሉ በሜዳ ላይ እንደምንሰጥ ያውቃሉ “ ሲል ለደጋፊዎች መልዕክቱን አስተላልፏል።

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Address


Addis Ababa
Addis Ababa
1000