Foot Ball Live 107.8 እግር ኳስን በቀጥታ

Foot Ball Live 107.8 እግር ኳስን በቀጥታ

Share

Foot ball Live streaming on radio.

14/09/2025

At The age of 40 with this new Club The Midfield Maestro keep shining and keep tasting better like fine wine 🍷

06/05/2023

አስደናቂው ጎል ጨራሽ የሲዝን ሪከርድ በጨበጠበት ምሽት ይከብዳቸዋል የተባሉትን መዶሻዎቹን ቀለል አድርገው የረቱት ሲትዝኖቹ በ6 አመት ለ5ኛ ጊዜ በተከታታይ ደግሞ ለሶስትዮሽ ምናልባትም የከተማ ተቀናቃኛቸውን የ99 ገድል ለመድገም የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰዋል በሳምንቱ አጋማሽ ከማድሪድ ጋር ከሚኖራቸው ሲዝናቸውን ወሳኝ መርሀ ግብር በፊት ላለመውረድ የሚውተረተረውና በሊጉ ስመጥር እሳት የማጥፋት ልምድ ያላቸውን ቢግ ሳምን የቀጠሩትን ሊድስን ዛሬ ካሸነፉ ከሊግ ተፎካካሪያቸው አርሰናል የ4 ነጥብ ብልጫ ይኖራቸዋል በተለይም ነገ እጅግ አስገራሚ ፎርም ላይ የሚገኙት ማግፓይስ ለአርሰናል ቀላል ተጋጣሚ ይሆናል ተብሎ አይገመትምና ሲቲዝኖቹ እድላቸውን ማበላሸት አይገባቸውም በአንጻሩ አሜሪካዊውን ጄሲ ማርችን ባለፈው የውድድር ዘመን በመቅጠር ከመውረድ የተረፈው ሊድስ ዘንድሮም ተመሳሳይ እጣ ገጥሞታል ይወጡት ይሆን
ፈታ ዘና በሽልማት የተንበሸበሸ ቆይታ ይኖረናል
ስፖንሰራችን አዲስ አበባን ለማወቅ ሮጣለሁ በቲሸርቶች ያንበሸብሻችኋል ተሳተፉ ቲፎዞ ግብግብም ሳይረሳ 10፡00 ላይ ቀጠሮ ይኑረን

Photos from Foot Ball Live 107.8 እግር ኳስን በቀጥታ's post 19/03/2023

ቀለል ያሉ የመሰሉ ተጋጣሚዎቹን በባከነ ሰአት ረትቶ ይፈተናል በተባለበት ክሬቨን ኮቴጅ ጎጆዎቹን አፈራርሶ ያቀለለው መድፉ በአውሮፓ ድጋሚ በቅርብ ቀርቷል ዋንጫውን ለመሳም ከፌቨራይቶች ተርታ የነበረው አርሰናል ባልተለመደ ሁኔታ በመለያ ምት ከመንገድ ቀርቷል ይህ በዋናነት በሁለት መልኩ ሲታይ ድካም በበዛበት በዚህ የውድድር ዘመን በሳምንት አንድ ጨዋታ ብቻ እየጠበቁ ማድረግ ጠባብ ስኳድ ላለው አርሰናል ለተጫዋቾቹ መጠነኛ እረፍትና ከጉዳት የራቀ ሲዝን እንዲያሳልፉ ከመርዳቱም በላይ ሙሉ ትኩረታቸውን ለ19 አመት የራቃቸውን ዋንጫ እንዲያደርጉ ያስችላል ሲባል በሌላኛው አንጻር በአውሮፓ ውጤታማ ከሆኑ እጅግ ለቁጥር የሚታክቱ አመታት ላለፉት አርሰናል ዘንድሮ ጥሩ አጋጣሚም ነበር ብለው የሚከራከሩም በርካታ ናቸው
ለመጨረሻ ጊዜ አርሰናል ወርቃማውን ዋንጫ ሲያሳካ ከፍ አድርጎ ያነሳው ፓትሪክ ቬራ ባለፈው የውድድር ዘመን በደርሶ መልስ ከአርሰናል ላይ የተሻለ ውጤት ይዞ ተመልሷል ዘንድሮ በመጀመሪያው አጋጣሚ በመድፈኞቹ ቢረታም አሁን ከሱ ዘመን በኋላ ላልሳሙት ዋንጫ እንቅፋት ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ በሴልሀርስት ፓርክ በተጫዋችነት እጅግ ጥቂት በአሰልጣኝነትም የተወሰነ ልምድ ከወሰደበት ሲቲ በሆላንድ ብቸኛ የፍቅም ጎል በጠባብ ውጤት ተሸንፎ ከክለቡ ጋር እህል ውሀው ማብቃቱ የተነገረው ከመድፈኞቹ ጋር ላለበት ጨዋታ በመዘጋጀት ላይ ሳለ ነው የስንብት ደብዳቤ የደረሰው ሽማግሌውን የቀድሞ የክለቡ አሰልጣኝ ሮይ ሆጅሰንን እሳት በጊዜያዊነት እንዲያጠፉ የመለሱት ንስሮቹ አርሰናልን ያነቅፉት ይሆን ወይስ መድፉ መተኮስ የሚችልበት ብቸኛ የውድድር ቀዳዳ ይህ ነውና እድሉን ይጠቀማል?? ከ10፡00 ጀምሮ አብረን ስንቆይ እየተዝናናን እንመለከተዋለን በቲክቶክ በዩቱብ እንዲሁም በብዙ የሶሻል ሚዲያ ፕላትፎርሞች የምታውቁትን የአርሰናል ደጋፊ እንግዳም እንጋብዛለን ሌላ ቀጠሮ እንዳትይዙ 10፡00 ሲል ኢትዮ ኤፍ ኤም ላይ

07/03/2023

እንኳን ማሸነፍ ጎል ማስቆጠር ተስኖት የከረመው ቼልሲ በሳምንቱ መጨረሻ ከረጅም የተከታታይ ውጤት አልባ ጉዞ በኋላ ማሸነፍ ተችሎታል ከ3 ሳምንታት በፊት ወደ ሲግናል ኢዱና ፓርክ አቅንቶ በቢጫ ግድግዳው ፊት አቀርቅረው የተመለሱት ሰማያዊዎቹ በጃንዋሪው የዝውውር ገበያ ከባድ ሸማች ሆነው ከየክለቡ አፍ የቀሟቸው የወደፊት ተስፈኛ ወጣቶች እስካሁን አልተቀናጁላቸውም ምናልባት ከአፎቻቸው የተቀሙት ክለቦች እምባ ይሆን?? 🤔🤔 በተከታታይ አዋራጅ ሽንፈት የገጠማቸው የብሪጅ ሰማያዊዎች በጥቅምት የቀጠሯቸውን አሰልጣኝ መንፈቅ እንኳን ሳይሞላቸው ስለማሰናበት እያሰቡ እንደሚገኙ ሹክሹክታዎች ያሳብቃሉ
በአንጻሩ ባልተለመደ ሁኔታ ትልቁን የጀርመን ቡጢኛ ሙኒኽና የዘንድሮውን ክስተት ዩኒዮን በርሊንን አጅበው በቡንደስሊጋው አናት ላይ ፊጥ ያሉት ቢጫዎቹ ከ2012 ወዲህ በአውሮፓ የምር ትኩረት የሚስብና ተፎካካሪ ቡድን በተከታታይ በማርኮ ሮዘ ስር የተጀመረው ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ ጎልብቶና ጎምርቶ በኤዲን ቴርዚች ስር ፍሬውን እያሳዩን ይገኛሉ ከ2012 ወዲህም ሩብ ፍጻሜውን ለመቀላቀል ሁነኛው ቡድን ለመሆን ቆርጠዋል ምንም እንኳን ችግር ላይ የሚገኘውን ቼልሲን በጠባብ ውጤት ተፈትነው ቢያሸንፉም ከአመት አመት ከሚደርሷቸው ተጋጣሚዎች አንጻር የአሁኑ ቼልሲ ለመጣል ቀላሉ ይመስላል ምን ያሳዩናል ቼልሲ የማሸነፍ ሂደቱን የምር ጀምሯል ወይስ ቢጫዎቹ ጥሩ ሲዝናቸውን የበለጠ ከፍ ያደርጉታል ከ3፡30 ጀምሮ በኢትዮ ኤፍ ኤም እንከሰታለን እንፍታታለን ጠብቁን

Photos from Foot Ball Live 107.8 እግር ኳስን በቀጥታ's post 05/03/2023

በአንፊልድ ከመሪነት ተነስቶ በማድሪድ የተደቆሰው ሊቨርፑል በታላቁ የእንግሊዝ ሃያላን ደርቢ አጀማመሩ መጥፎ የነበረው ዩናይትድ በቀዮቹ ላይ በመረማመድ ነበር ሲዝናቸውን ያቃኑት የመርሲሳይዱ ቀይ አምና ለአራት ዋንጫ እስከ ፍጻሜው እንዳልተባጠሰ ዘንድሮ ግን እንኳን ዋንጫ ዋንጫ አካባቢም ላንመለከተው እጅጉን ርቆ ተስፈንጥሯል በኦልድትራፎድ ሁለቱ ቡድኖች በሴፕተምበር ሲገናኙ በተቀራራቢ መጥፎ አቋም ላይ የነበሩ ሲሆን ከዚያ ወዲህ ነገሮች ተገለባብጠው ቀዮቹ ሰይጣኖች እጅግ ጎምርተዋል
የክሎፕ ሰራዊት ሰሞነኛ መነቃቃት ቢያሳዩም ማድሪድ አስጎንብሷቸው ፓላስ ወጥሯቸው የነበረ ቢሆንም ተኩላዎቹን ሞተ ሞተው በማሸነፍ እንጥፍጣፊ የማሸነፍ ደመ ነፍሳቸው አብሯቸው እንዳለ ያሳብቃል በመጪው ማክሰኞ ወደ ማድሪድ የሚያቀኑት ቀያዮች ብዙም ተስፋ ለሌለው የአውሮፓ መድረክ ቀጣይ ጉዞ ብለው የዛሬውን ጨዋታ ይሰዋሉ ተብሎ አይገመትም ምንም እንኳን ከዚህ ቀደም ባርሴሎናን እንዲሁም በኢስታንቡል ሚላንን ከ3 ጎል የበታችነት ተነስተው ቢያስከነዱም አሁን ባላቸው ወቅታዊ አቋምና በማድሪድ በተደጋጋሚ በመሸነፍ በተወሰደባቸው ስነልቦናዊ የበላይነት ወደ ማድሪድ ሄደው የተሻለ ነገር ይዞ ለመመለስ ከተዓምር በላይ ያስፈልጋቸዋል።
በአንጻሩ ከሴፕቴምበሩ ግጥሚያ ወዲህ እጅግ የጎለበተው ማን ዩናይትድ ከ6 አመት በኋላ ዋንጫ ከመሳሙም በላይ እጅግ የሚታይ ፍሬያማ ለውጥ አሳይቷል የተዋቀረ ቡድን መሆኑንም ያለማቋረጥ ረቡዕ እሁድ ረቡዕ እሁድ እያደረገም በብዛት በአሸናፊነት ተወጥቷል በሳምንቱ አጋማሽ ጭምር የመጀመሪያ አጋማሽ ላይ የተዳከመ የመሰለው ሰይጣኑ የኋላ ኋላ እጅግ ልዩ በመሆን መዶሻዎቹን አቅልጧል አሁንም 4 ዋንጫዎችን በርቀት እያየ የሚጓዘው ቡድን ነው
ያም ሆነ ይህ የቀዮቹ ባላንጣነት ከደርቢ ተቀናቃኞቻቸውም በላይ በሁለቱ መሀል ያይላልና በውጤታማነትም ከፍ ያሉት ሁለቱ በእንግሊዝ ከፍ ያለ ፓለቲካዊና ታሪካዊ ተቃርኖ ታጅቦበት የሚደረግ ትንቅንቅ ነውና ስሜቱ ይለያል
ባለፉት ሁለት አመታት የመርሲሳይዱ ቀዮች በሰይጣኖቹ ላይ ሙሉ የበላይነት ተቀናጅተው በቲያትር ኦፍ ድሪምስ ጭምር የቀድሞውን ሂሮ ኦሌን በጣም ባስወገዘ መርሀ ግብር 5 ለምንም ረምርመዋቸውል ያንን የደርሶ መልስ ተከታታይ አመታት ሽንፈት ለመበቀል ጥሩ ቁመና ላይ ቢገኙም የክሎፕ ሰራዊት ቢሞቱ ቢደክሙም ለማንችስተሮች እንደማይደክሙ ከሲቲ ጋራም ጭምር አስይተውናል ይህ ሁሉ ተጠባቂ ክስተት ያለበት ትንቅንቅ ወደናንተ ይዘን ለመከሰት ዝግጅታችን ተጠናቋል ከናንተ የሚጠበቀው ሬዲዮኖቻችሁን ከፍታችሁ ጆሮዎቻችሁን እንድታውሱን ተሳትፎአችሁም እንዳይለየን ብቻ ነው በቲፎዞ ግብግብ ታጅበን ከ12፡30 ጀምሮ እንከሰታለን በቲክቶክም ጠብቁን ትዝናናላችሁ

04/03/2023

የሊጉ መሪ አርሰናል ተስተካካዩን ማሸነፉን ተከትሎ ከአሁን በኋላ መደናቀፍ የማይፈቀድለት ማንሲቲ ባለፈው ሳምንት ወደትልቅነት እየተንደረደረ መሆኑን ከ24 አመት በኋላ የፍጻሜ ተፋላሚ በመሆን ያሳየውን ኒውካስልን ይገጥማል በግልባጩ ጨዋታ እጅግ አስገራሚ በነበረው በመሃከለኛው ምስራቅ ከበርቴዎች ባለቤትነት የተያዙት ሁለት ቱጃሮች አንደኛው በፕሪምየር ሊጉ ዋንጫዎች አሸብርቆ ሲገኝ በFFP ግን ያላግባብ ነው በሊጉ ከፍ ያልከው የሚል ውንጀላ እየናጠው ይገኛል በአንጻሩ በሀብታሞቹ ሞናርኪዎች የተጠቀለሉት ማግፓይሶች ቀድመው ላለማጋበስ በተጠና መንገድ ወደከፍታ እየከነፉ ይመስላል
በሊጉ የተደላደለው ሲቲና አዲሱ Emerging Power ኒውካስል በኤል ካሺኮ ወይም በፔትሮል ስቴሽን ደርቢ ከ9፡00 ጀምሮ ይፋጠጣሉ ኒውካስትል ካለፉት ሳምንታት ሸርተት ማለቱ በመንቃት በስፐርስ የተወሰደበትን የቶፕ 4 ለማስመለስ በአንጻሩ ባለሜዳው ካሁን በኋላ ከተደናቀፈ የመድፈኞቹ ተኩስ አይደረስበትምና ከኋላ ከኋላ በመከታተል ለማስጨነቅ የሚያደርጉት ግብግብ ይዘን እንከሰታለን በቲክቶክም አለን ጠብቁን::

02/03/2023

እንኳን ለ127ኛው የአገራችን የመላው ጥቁር ህዝቦች እንዲሁም በባርነት ቀንበር ስር ለነበሩ ሁሉ የተስፋ ውጋጋን ለፈነጠቀው የድል በዓላችን በሰላም አደረሳችሁ

01/03/2023

ሾን ዳይችስ ለቶፊዎቹ እሳት አጥፊ ሆነው መምጣታቸውን ተከትሎ መድፈኞቹ አስገራሚ የነበረ ጉዟቸው ተንገራግጮ ነበር በኤሚ ማርቲኔዝ እድለቢስ አጋጣሚ የፌብሩዋሪ የመጀመሪያ ድላቸውን አሳክተው ሌስተርንም አጣጥመዋል ከሲቲ ጋር ያለ ልዩነታቸውን ለማስፋት ይዘዋት የቆዩት ተስተካካይ ጨዋታቸውንም የጉዲሰኑንም ሽንፈት ለመበቀል በኤምሬትስ ምሽት ላይ ኤቨርተንን መድፋቸውን ስሌ ይጠብቃሉ
በአንጻሩ ከላምፓርድ ከተለዩ በኋላ ግትሩን እንግሊዛዊ የቀጠሩት ቶፊዎቹ ሁለት አሸንፈው በደርቢውና በአስቶን ቬላ ተረትተው ከወራጅ ቀጠና ብዙም አልራቁም ዛሬስ ምን ያሳኩ ይሁን መድፈኞቹን በማደናቀፍ ለሲቲ ውለታ ያደርጉ ይሆን ምሽት 3፤00 እንገናኝ

Photos from Foot Ball Live 107.8 እግር ኳስን በቀጥታ's post 27/02/2023

Undeniably Unarguably The Bests Again

23/01/2023

በትላንቱ የአርሰናል ድል ጮቤ የረገጠውና በቲፎዞ ግብግብም የሚታይ ብልጫ የወሰደው አርቲስት Mulugeta በቡድንህም ድል በነበረንም ግሩም ቆይታ አስገራሚ ምሽት አሳልፈናል ክብረት ይስጥልን ⚽️⚽️⚽️🤝🤝

Photos from Foot Ball Live 107.8 እግር ኳስን በቀጥታ's post 22/01/2023

“The Battle of Old Foe’s”

ምናልባትም በእኛ አገር የእግር ኳስ ትንቅንቅ ታሪክ በአብዛኛው የስፖርት ተከታታይ ማህበረሰብ ዘንድ ከየትኛውም ደርቢ በላይ በደጋፊ ግብግብ ለረዥም ዘመን ላቅ ያለ ፉክክር እና ግብግብ እያየን አድገናል በአርሰን-ፈርግሰን የአሰልጣኝነት ዘመን ጣራ የነካው የትንቅንቅ ስሜት ከእንግሊዝ ተሻግሮ መላው አለምን ሲያዳርስ በኢትዮጵያም የሱፐር ስፖርት ስርጭት መጀመሩን ተከትሎ ብዙዎችን በፕሪምየር ሊጉ ፍቅር ወድቀዋል በዋነኝነት በወቅቱም ሀያል የነበሩትና ማን ዩናይትድ በስፋት ደግሞ አርሰናል በኢንቪንሲብል ሲዝኑ ብዙዎችን መማረክ ችለዋል በተለይ የሬይ ፓርለርና የነ ቫንኒስተልሮይ ፍጥጫ እንዴት ይረሳል ኪን ከ ቬራ፤ ኔቭል ከነ አሽሊ፤ ኮል ኦነሪ ከቫን ኒስተልሮይ፤ ከምንም በላይ ከጨዋታው በፊትና በኋላ በሰሩና በፕሮፌሰሩ መሀከል ያሉ ሽንቆጣዎች ልዩ ትኩረት በሚስብ መልኩ እንድናስታውስ በጥሩ ትውስታ አሳድገውናል እስቲ የናንተንም ትውስታ አጋሩን
ለረጅም ጊዜ የሁለቱ ቡድኖች ፍጥጫ በደጋፊው ልብ ከፍ ያለ ቦታ ይያዝ እንጂ የቡድኖቹ የፉክክር ጨዋታ እዚህ ግባ የሚባል አልነበረም ወይ አንደኛው የተሻለ የበላይነት ኖሮት አለዚያም ሁለቱም በጥሩ አቋም ላይ እያሉ የተደረገ ጨዋታ ለማስታወስ ከአስር አመት በላይ ወደ ኋላ መመለስ የግድ ይለናል እጅግ በአስገራሚ የውጤት ግስጋሴ ላይ የሚገኙት የአርቴታ መድፈኞች ሂደቱን አምነው ለአመታት የተናፈቀው አርሰናል በግሩምና አሳማኝ ጨዋታ መደፋቸውን ስለው ከእቅድ በላይ በመተኮት ለናፈቁት የሊግ ክብር አልመዋል እስካሁን የተደናቀፉት ኦልድትራፎርድ ብቻ ነው በአንጻሩ አጀማመሩ ከባድ የነበረው ቀያይ ሰይጣኖቹ አለቃ ቴን ሀግ ነገሮችን ለማስተካከል ጊዜ ቢፈልግም ወደ ትክከለኛው ትራክ የገቡ መስለዋል ወሳኙ ካዝሜሮ እጅግ በቀሽም ውሳኔ በፓላሱ ጨዋታ በተመለከተው ቢጫ ካርድ የዛሬዉ ጨዋታ የሚዘለው መሆኑ ለብዙ ዩናይትዳዊያን ስጋት ቢጤ ገብቷቸዋል በኦልድትራፎርዱ ጨዋታ ፓርቴን ያጡት አርሰናሎች ምናልባትም ለመጀመሪያ ጊዜ በጥሩ ልበ ሙሉነት ዩናይትድን ለመበቀል ጭምር ያስተናግዳሉ ማሸነፍ ከቻሉ ከተከታዮቻቸው ያላቸውን ልዩነት ቢያንስ ማስጠበቅ ሲችሉ ሲቲ በተኩላዎቹ ነጥብ ከጣለ ዋንጫው ላይ አንድ እጃቸውን ያሳርፋሉ።
እናንተም ይህን ተጠባቂ ጨዋታ በቲፎዞ ግብግብ እየተተራረብን እየተሸነቋቆጥን ከተጋበዙት ደጋፊዎች ጋር ግሩም ጊዜ ይኖረናል በቲክቶክም በቀጥታ ቀጠሮ ይኑረን 1:00 በኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 እንገናኝ [email protected]

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Telephone

Website

Address


Adiss Ababa
Addis Ababa