Ethio-Kickoff

Ethio-Kickoff

Share

Ethio-Kick off is First Ethiopian Sports news platform, connecting Ethiopian Soccer, Athletics fans and readers through a social media . 📱📲#
.

Our mission is simple: - To provide all kinds of local sports.🎤🔊💻

Photos from Ethio-Kickoff's post 30/08/2026

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በታንዛንያ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው ከ20 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የሴካፋ ማጣርያ ዝግጅቱን በዛሬው ዕለት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጀምሯል።

በዋናው ብሔራዊ ቡድን ዝግጅት ላይ ተካተው የነበሩትን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች በመጀመርያው የልምምድ መርሐ ግብር ላይ የተገኙ ሲሆን ከስብስቡ መካከል በጴጥሮስ ተሾመ ምትክ የኢትዮጵያ ቡናው የአብሥራ አስናቀ ተተክቷል።

29/08/2026

⭕️ በካፍ የሴቶች ቻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ እየተካፈለ የሚገኘውየምድብ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዛሬ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ አድረገው የጨዋታ የሙሉ ሰአት ውጤት
👇🏽
ካዌምፔ ሙስሊም ሌዲስ 3 - 0 ንግድ ባንክ
17' ጆቪያ ናካጎሎ
55' ትእግስት አዳነ (በራሷ ላይ)
73' አግኔስ ናቡኬንያ

25/08/2026

⭕️ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተቀየረው ደንብ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅሏል

👇🏽

በሴቶች የአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ የምድብ አንድ ጨዋታዎች ከተጠናቀቁ በኋላ ንግድ ባንክ ከምድብ ማለፉን አረጋግጧል።

አስቀድሞ የነበረው የውድድሩ ደንብ አራት ቡድኖችን ከያዘው ምድብ አንድ ሁለት ቡድኖች ሶስት ቡድኖችን ከያዙት ምድብ 2 እና 3 ደግሞ አንድ አንድ ቡድኖች ያልፋሉ የሚል ነበር።

ነገር ግን ውድድሩ ከተጀመረ በኋላ በተሻሻለው ደንብ መሰረት ከሶስቱም ምድቦች አንደኛ ሆነው ያጠናቀቁ ወደ ግማሽ ፍፃሜው አልፈው ከሶስቱ ምድቦች ጥሩ 2ኛው አራተኛው የግማሽ ፍፃሜ ቡድን ይሆናል።

በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በቅዳሜው ጨዋታ ያስቆጠራቸውን 11 ግቦች ተከትሎ ወደ ግማሽ ፍፃሜ ማለፉን አረጋግጧል።

ነገ በሚደረገው የምድቡ ጨዋታ ካዌምፔ ሙስሊም ሌዲስ የጅቡቲውን ዩጄኮ ካሸነፈ ወይም አቻ ከተለያየ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በግማሽ ፍፃሜው ከራሱ ከካዌምፔ ሙስሊም ሌዲስ ጋር ይገናኛል።

ዩጄኮ ካዌምፔ ሙስሊም ሌዲስን ማሸነፍ ከቻለ ደግሞ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከዩጄኮ ጋር ለፍፃሜ ለማለፍ ይጫወታል።

የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታው ቅዳሜ 07:00 ጀምሮ ይደረጋል።

Photos from Ethio-Kickoff's post 25/08/2026

በሴፕቴምበር ወር በሚካሄዱ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ እና ኢንተር-ክለብ ውድድሮች ላይ በካፍ የተመደቡ ኢትዮጵያውያን የጨዋታ አመራሮች

Photos from Ethio-Kickoff's post 24/08/2026

⭕️በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የፀደቁ ውሎች

የኢትዮጵያ ወንዶች ፕሪምየር ሊግ

ሰኞ ነሐሴ 18/2018

Photos from Ethio-Kickoff's post 24/08/2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ የሚያደርገውን ዝግጅት በመቀጠል በዛሬው ዕለት የዘጠነኛ ቀን ልምምዱን በአዲስ አበባ ስታዲየም በጠዋት እና ከሰዓት መርሐ ግብር አከናውኗል።

ከቡድኑ ስብስብ መካከል ነፃነት ገብመድህን በአፍሪካ ውድድር የሚሳተፈው ወልዋሎን በመቀላቀሉ በአሁኑ ወቅት 30 ተጫዋቾች ዝግጅት እያከናወኑ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በዛሬው መርሐ ግብር ተገኝተዋል።

24/08/2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ የምድብ 10 የመጀመርያ ጨዋታ ሱዳንን የሚገጥምበት ቀን እና ቦታ ታውቋል።

የሱዳን እግር ኳስ ማኅበር የሜዳውን ጨዋታ ለማድረግ የደቡብ ሱዳኑ ጁባ ናሽናል ስታዲየምን መምረጡን አሳውቋል። በዚህም መሠረት ጨዋታው ዓርብ መስከረም 15 ቀን 2019 ዓ/ም ምሽት 1:00 ላይ ይካሄዳል።

24/08/2026

ኢትዮጵያ የ2028ቱን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ ጥያቄዋን ያቀረበችበት ሰነድ (Bid Document) ለአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) አስገባች::

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከኢፌዴሪ መንግሥት ጋር በጋራ አስፈላጊ ዶክመንቶችን ያካተተ ሰነድ (BID HAND BOOK) ለካፍ በማስገባት ይህንን ታላቅ አህጉራዊ የእግር ኳስ ድግስ ለአራተኛ ጊዜ በስኬት ለማስተናገድና በአፍሪካ እግር ኳስ ያላትን ጉልህ ታሪክ ዳግም ለማደስ ዝግጁነቷን አረጋግጣለች ሲል ፌዴሬሽኑ አስታውቌል።

24/08/2026

⭕️ የሙሉ ሰአት ውጤት

በካፍ የሴቶች ቻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ እየተካፈለ የሚገኘውየምድብ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የምድቡን ሁለተኛ ጨዋታ

👇🏽
ካዌምፔ ሙስሊም ሌዲስ 1 - 0 ኢትዮ-ንግድ ባንክ
አግኔስ ናቡኬንያ (ፍ)

Photos from Ethio-Kickoff's post 24/08/2026

⭕️ዕረፍት

በካፍ የሴቶች ቻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ እየተካፈለ የሚገኘውየምድብ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የምድቡን ሁለተኛ ጨዋታ እያደተገ ይገኛል።

ካዌምፔ ሙስሊም ሌዲስ 1 - 0 ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
አግኔስ ናቡኬንያ (ፍ)

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Address


Old Airport
Addis Ababa