09/06/2026
♦️የቃላት ስስት ሳይታይባችሁ ፍቅራችሁንና መልካም ምኞታችሁን የገለፃችሁልኝን፣በልባችሁ መልካሙን የተመኛችሁልኝን በሙሉ ዝቅ ብዬ አመሠግናለሁ።
🛩️✈️አሁን ጉዞ ወደ ቶሮንቶ ጀምረናል
✈️በኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ET552 በቀጥታ ሮም ቶሮንቶ
ሮም ጣሊያን ለመድረስ ⏰ 5:40 የሚወስድ ሲሆን
40,000 ጫማ ከፍታም እንበራለን
እግር ኳስን ከምንጩ መጠጣቴን ቀጥያለሁ
09/06/2026
🏆🏆🏆 ጉዞ ወደ ታሪካዊው የዓለም ዋንጫ 🏆🏆🏆
🏆🏆🏆 የዓለም ዋንጫ ሀትሪክ 🏆🏆🏆
🇿🇦 2010 ደቡብ አፍሪካ
🇶🇦2022 ኳታር
2026 ሜክሲኮ፣ካናዳ፣አሜሪካ
♦️ከሆነልኝ ሁሉ አንዳች እንኳ ከድንግል ማርያም ልጅ መድኃኒያለም ውጭ የሆነ የለም
🙏🙏ተመስገን🙏🙏
🙏🙏ስለሆነው ነገር ሁሉ እግዚያብሄር ክብሩን ይውሠድ🙏🙏
09/06/2026
♦️ማንችስትር ዩናይትድ ኤልየት አንደርሰንን የማስፈረም ተስፋ መሰነቁ ተነገረ
✍️✍️በጋዜጠኛ ሳምሶን አበበ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
የኦልድትራፎርዱ ክለብ የኖቲንግሀም ፎረስት እና እንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን አማካይ ኤልየት አንደርሰን ፊርማ ከከተማ ተቀናቃኙ ማንችስትር ሲቲ በመብለጥ እንደሚያገኝ ተስፋ መሰነቁ ተዘግቧል።
የ23 አመቱ ተጫዋች በክረምቱ የዝውውር መስኮት ሲቲ ግራውንድን ሪከርድ በሆነ የዝውውር ሂሳብ ሊለቅ እንደሚችል በተደጋጋሚ ጊዜ ሲዘገብ መቆየቱ ይታወሳል።
ማንችስትር ሲቲ ቀደም ብሎ ለአማካዩ ያቀረበው 80 ሚሊየን ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ በፎረስት ውድቅ እንደተደረገበት ይታወቃል።
የዩናይትድ እግር ኳስ ዳይሬክተር ጄሰን ዊልኮክስ አማካይ ክፍሉን ለማጠናከረ ከአንደርሰን በተጨማሪ በዌስትሀም ዩናይትዱ ማቲያስ ፈርናንዴስ ላይ አይናቸውን ማሳረፋቸው ተነግሯል።
09/06/2026
♦️አርሰናል ትኩረቱን በሞርጋን ጊብስ ዋይት ላይ ማድረጉ ተገለጸ
✍️✍️በጋዜጠኛ ሳምሶን አበበ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
የሰሜን ለንድኑ ክለብ የኖቲንግሀም ፎረስቱን ኮከብ ለማስፈረም በጥብቅ እየሰራ መሆኑ ተነግሯል።የሚኬል አርቴታ ቡድን የፕሪምየር ሊግ ክብሩን በቀጣይ አመትም ለማስጠበቅ በክረምቱ የዝውውር መስኮት የነቃ ተሳትፎ እንደሚያደርግም ይጠበቃል።
እንደ ዘ ሰን የወሬ ምንጭ ዘገባ የ26 አመቱ ጊብስ ዋይት በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን በፎረስት ቤት ያሳየው ድንቅ ብቃት የታላላቆቹን የአውሮፓ ክለቦች ትኩረት እንዲስብ አድርጎታል።
ዋይት በሁሉም መድረክ ውድድሮች በ2025-26 በ53 ጨዋታዎች 18 ጎሎችን ሲያስቆጥር ሰባት የጎል ኳሶችን ደግሞ ለቡድን አጋሮቹ አመቻችቶ አቀብሏል።
09/06/2026
♦️የቀድሞ የሪያል ማድሪድ እና ስፔን ብሄራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ከሜሲ እና ሮናልዶ ጋር ተያይዞ ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ ሰጥቷል
✍️✍️በጋዜጠኛ ሳምሶን አበበ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
ኢከር ካሲያስ በስፔኑ ዋና ከተማ ክለብ ውስጥ ወርቃማ የእግር ኳስ ህይወት ከነበራቸው ተጫዋቾች መካከል አንዱ እንደነበር የሚታወስ ነው።
ካሲያስ ከፖርቱጋላዊው እና አርጀንቲናዊው ኮከብ ጋር ተያይዞ የትኛው ፈታኝ ተፋላሚ ነው ? በሚል ለቀረበለት ምላሽ ሰጥቷል።
"ከሮናልዶ ጋር በክለብ ደረጃ በተቃራኒ አልተጫወትኩም ። የተገናኘሁት በብሄራዊ ቡድን ነው።
እንደማስበው ግን ሜሲ ይበልጥ አስቸጋሪ ነው።" ሲል ምላሹን ሰጥቷል።
09/06/2026
♦️ብራዚል ከኔይማር ጉዳት ጋር ተያይዞ ወቅታዊ ሁኔታውን በተመለከተ መረጃ ይፋ አድርጋለች
✍️✍️በጋዜጠኛ ሳምሶን አበበ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
የብራዚል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከሁለት ቀናት በኋላ በይፋ ከሚጀመረው የአለም እግር ኳስ ዋንጫ ቀደም ብሎ ስለ ኮከቡ የጉዳት ሁኔታ ወቅታዊ መረጃን አጋርቷል።
የ34 አመቱ ኔይማር ለሴሌሳኦዎቹ ለመጨረሻ ጊዜ ጨዋታ ካደረገ ሶስት አመት ሊደፍን የተቃረበ ቢሆን ጣልያናዊው አሰልጣኝ ካርሎ አንቼሎቲ ተጫዋቹ ከባት ጉዳቱ ጋር እየታገለም በአለም ዋንጫው የቡድን ስብስባቸው ውስጥ አካተውታል።
እግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ሰኞ ምሽት የMRI ምርመራ እንደተደረገለት አስታውቆ የማገገም ሂደቱ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሆነ ገልጿል።
08/06/2026
♦️አፍሪካዊው ኢንተርናሽናል አርቢትር ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ መከልከላቸው እያነጋገረ ነው
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
የ2025ቱን የካፍ ቻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታን የመሩት እና በ2025 የአፍሪካ ምርጥ ዳኛ ተብለው የተመረጡት ሶማሊያዊው ኢንተርናሽናል አርቢትር ኦማር አርታን በአፍሪካ እግር ኳስ ውድድር ባሳየው ድንቅ የዳኝነት ብቃት እና ባለው ስኬታማ ሪከርድ አለም ዋንጫን እንዲመራ በፊፋ መመረጡ አይዘነጋም።
የምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ሶማሊያ በአሜሪካ የጉዞ እገዳ ዝርዝር ውስጥ በመሆኗ ሶማልያዊው ኢንተርናሽናል አርቢትር ኦማር አርታን ቪዛ ለማግኘት ችግር ገጥሞት እንደነበር ዘገባዎች ያስረዳሉ።
በኬንያ የሶማሊያ ኤምባሲ ባደረገው ጥረት ወደ አሜሪካ እንዲገባ ይፈቀድልኝ በሚል ጥያቄ እንዳቀረበና የዲፕሎማቲክ ፓስፖርት እንደተሰጠው ነው የተሠማው።
ነገር ግን ኢንተርናሽናል አርቢትር ኦማር አርታን ሚያሚ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እንደደረሰ ወደ አሜሪካ ድንበር እንዳይገባ ከመከልከል ባለፈ ወደተነሳበት ሀገር መባሉና ወደ ቱርክ እንደተመለሠ ነው የተዘገበው።
በድርጊቱ እጅጉን የተበሳጩት የሶማሊያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አመራሮች ጉዳዩን ወደ ፊፋ በመውሠድ አቤት እንዳሉ የተነገረ ሲሆን በዚህም በርካቶች የአለም እግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል ምን አይነት እርምጃ እንደሚወስድ ለማየትም እየጠበቁ ነው።
በሶማሊያዊው ዳኛ ላይ ደረሠ የተባለው ድርጊት እውነት ተፈፅሞ ከሆነ በአፍሪካ እግር ኳስ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ለደረሰው ዳኛ በሙያው የህይወቱ እጅግ ተስፋ አስቆራጭ ሁኔታ ሆኖ ይመዘገባል መባሉም ነው እየተሠማ ያለው ።
ሶማሊያዊው ኢንተርናሽናል አርቢትር ኦማር አርታን በዕገዳ ምክንያት ከዓለም ዋንጫው ውጪ በመሆኑ በዓለም ዋንጫ መድረክ የዳኘ የመጀመሪያው ሶማሊያዊ በሚል በታሪክ የመመዝገብ ዕድሉንም አጥቷል።
08/06/2026
♦️ጁሪየን ቲምበር በብሽሽት ጉዳት ምክንያት ከአለም ዋንጫ ውጭ ሆነ
✍️✍️በጋዜጠኛ ሳምሶን አበበ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
የአርሰናል እና ኔዘርላንድ ብሄራዊ ቡድን ተከላካይ የፊታችን ሀሙስ ከሚጀምረው የአለም እግር ኳስ ዋንጫ በብሽሽት ጉዳት ምክንያት ውጭ መሆኑን የሀገሪቱ እግር ኳስ ማህበር ይፋ አድርጓል።
ቲምበር ጉዳቱን በመጋቢት ወር ማስተናገዱ የሚታወስ ሲሆን ለረጅም ጊዜ ከሜዳ ከራቀ በኋላ በቻምፒየንስ ሊጉ ፍጻሜ ቡድኑ በመለያ ምት በፒኤስጂ በተረታበት ጨዋታ በሁለተኛው አጋማሽ ተቀይሮ ወደ ሜዳ መግባት ችሎ ነበር።
የደች እግር ኳስ ማህበር የ24 አመቱ ተጫዋች ሙሉ ለሙሉ ከጉዳቱ አለማገገሙን አስታውቆ በአለም ዋንጫው መጠቀም ከህክምና ጉዳዮች ጋር ተያይዞ ተገቢ እንዳልሆነ መረዳቱን አስታውቋል።
08/06/2026
♦️ሞሮኮ ከኳታር ስኬቷ በኋላ በዓለም ዋንጫ ሌላ አዲስ ታሪክ ስለመስራት ታስባለች
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
የሠሜን አፍሪካዊቷ ሀገር ሞሮኮ በ2022ቱ የኳታር የዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት ሀገር በመሆን በሰሜን አሜሪካ ወደ ሚካሄደው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሌላ አዲስ ታሪክ ለማፃፍ ተጉዛለች።
የአትላስ አንበሶች የአፍሪካን እግር ኳስ ታሪክ ከአራት አመታት በፊት በመቀየር፣ የአለማችን ጠንካራ ቡድኖችን ጭምር በማሸነፍ እና የአህጉሪቱ ቡድኖችም በአለም ዋንጫው በጥንካሬና በውጤት መጓዝ እንደሚችሉ በተግባር አሳይተዋል።
የመሀመድ ኡዋህቢ ቡድን በተጠባቂው የአለም ዋንጫ በምድብ ሲ ከብራዚል፣ ከስኮትላንድ እና ከሄይቲ ጋር ተደልደለው ውድድራቸውን በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።
በኒውዮርክ(ኒው ጀርሲ) ከብራዚል ጋር የሚያደርጉት የመክፈቻ ጨዋታ ቀላል ይሆናል ተብሎ የማይጠበቅ ቢሆንም ሞሮኮ በዓለም ዋንጫ ታሪክ ስኬታማ ከሆነችው ሀገር ጋር እንድትመዘን እድል ይሰጣታል።
ለአፍሪካ ታዳሚዎች የሞሮኮ ወደ ዓለም ዋንጫው መመለስ ልዩ ትርጉም አለው፤ የ2022 ሩጫቸው የሞሮኮ ስኬት ብቻ አልነበረም፤በመላው አፍሪካ የሚገኙ ደጋፊዎች በአለም ዋንጫው ላይ የነበረው መሰናክል እንደተሰበረ እንዲገነዘቡ ያደረገም ነበር፤በዚህ ስኬታማ ጉዞ ውስጥ ካሉት ቁልፍ ሰዎች አንዱ የሆነው ቡኑ ሞሮኮን ወደ ግማሽ ፍፃሜው ያደረሰው መሰረት አሁንም እንዳለ ያምናል። ግብ ጠባቂው ያሲን ቡኑ "የተጫዋቾች ጥራት አሁንም አብሮን አለ" ሲል ለፊፋ ድረ-ገፅ ተናግሯል።
ትክክለኛው አስተሳሰብም እንዲሁ ይሆናል ምክንያቱም ይሄ የዓለም ዋንጫ ነው ፣ እያንዳንዱ ተጫዋች በዓለም ዋንጫ የመጫወት ብቻ ሳይሆን ታሪክ የመስራት ህልም አለው፣ለአንዳንዶች ይህ ምናልባት የመጨረሻው የዓለም ዋንጫቸው ሊሆን ይችላል ለሌሎች ደግሞ የመጀመሪያ፤ ያ የልምድ ድብልቅ እና ትኩስ ጉልበት ለሞሮኮ ተስፋዎች እንደ ጥሩ አጋጣሚ ሊወሠድ ይችላል። ሞሮኮ ከኳታር ስኬቷ በኋላ በዓለም ዋንጫ ሌላ አዲስ ታሪክ ስለመስራት ማሰቧን ባለማቆሟ ተጋጣሚውቿ አቅልለው አይመለከቷትም።