30/05/2026
ሊቨርፑል አሠልጣኝ አርነ ስሎትን አሰናበተ
ሊቨርፑል ኔዘርላንዳዊውን አሠልጣኝ አርነ ስሎትን አሰናብቷል። አርነ ስሎት በሊቨርፑል ቤት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማሳካት ችለው ነበር።
በዚህ ገጽ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል
ሀገራዊ እና አለማቀፋዊ
ወቅታዊ እና ትኩስ የስፖርት መረጃዎች ይቀርቡበታል
30/05/2026
ሊቨርፑል አሠልጣኝ አርነ ስሎትን አሰናበተ
ሊቨርፑል ኔዘርላንዳዊውን አሠልጣኝ አርነ ስሎትን አሰናብቷል። አርነ ስሎት በሊቨርፑል ቤት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማሳካት ችለው ነበር።
26/05/2026
የቤጉ ሊግ የጥሎ ማለፍ ዋንጫ አሸናፊዎቹ ወረዳ አንድ አኞንሾ ድሉን በጋራ አክብረዋል
በቤጉ ሊግ የጥሎ ማለፍ ዋንጫ ቤጉ ፖሊሲን ያሸነፉት ወረዳ አንድ አኞንሾ የክለቡ አባላት እና አመራሮች በተገኙበት በቤንስ አይከን ሆቴል ወጣት ዘላለም እዮኤል ጋባዥነት የምሳ ግብዣ ፕሮግራም በማዘጋጀት ድሉን በጋራ አክብረዋል።
የክለቡ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ደግሞ ክለቡ ባስመዘገበው ውጤት በመደሰቱ ለክለቡ የ150 ሺህ ብር ድጋፍ አበርክቷል።
25/05/2026
ማንያዘዋል ጎዳዬ የባምበሲ ቤላአጉሩ እግርኳስ ክለብ አሰልጣኝ ሆነ
ከዚህ በፊት በቤጉ ሊግ የዱልአዛሃቢ አሰልጣኝ በመሆን የምናውቀው ማንያዘዋል ጎዳዬ በክልል ክለቦች ሻምፒዮና የሚሳተፈውን ባምበሲ ቤላአጉሩን ለማሰልጠን ፈርሟል።
24/05/2026
የአሶሳ ግብርና ቴክኒክ ትምህርት ስልጠና ኮሌጅ ዲን ሙስጠፋ ያሲን
የቤጉ ሊግ የማጠቃለያ ውድድር እና የጥሎ ማለፍ ዋንጫ እስከፍፃሜው ድረስ በአሶሳ ግብርና ቴክኒክ ትምህርት ኮሌጅ ሲካሄድ አብዛኛውን ጨዋታ ሜዳ በመገኘት ጨዋታውን የሚከታተሉ እና ኮሌጁ በመደበኛ ተልዕኮው በተጨማሪ በስፖርቱ ዘርፍ እያከናወነ ለሚገኘው ጅምር ስራ አሻራቸውን እያኖሩ የሚገኙ ናቸው።
ኮሌጁ ተደብቆ ከቆየበት እንዲነቃቃ ከማድረጋቸው ባለፈ በኮሌጁ ስም እግርኳስ ክለብ በመመስረት እንዲሁም ኮሌጁ ውድድሮችን እንዲያዘጋጅ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታ በማመቻቸት በምቹ መስተንግዶ ውድድሩ እንዲጠናቀቅ እሳቸውና የኮሌጁ አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች የነበራቸው ትጋት ቀላል አልነበረም።
በዛሬው ዕለት የተጠናቀቀውን የጥሎ ማለፍ ጨዋታ በቤጉ ስፖርት ቀጥታ ስርጭት ሽፋን እንዲያገኝ የኮሌጁ ዲን አቶ ሙስጠፋ ያሲን ስፖንሰር በማድረግ ለስፖርት ያላቸውን ስሜት በድጋሚ አረጋግጠዋል።
በቤጉ ስፖርት ስም እናመሰግናለን
24/05/2026
ወረዳ አንድ አኞንሾ ቤጉ ፖሊስን በመለያ ምት 5 ለ 4 በማሸነፍ የጥሎ ማለፍ ዋንጫ አሸንፏል
በቤጉ ሊግ የጥሎ ማለፍ ፍፃሜ ጨዋታ ወረዳ አንድ አኞንሾ ከ ቤጉ ፖሊስ መደበኛ ጨዋታ አንድ አቻ ተለያይተው አሸናፊውን ለመለየት ወደ መለያ ምት አምርተዋል
24/05/2026
በቤጉ ሊግ የጥሎ ማለፍ ውደድር ፍፃሜ ጨዋታ ወረዳ አንድ አኞንሾ ከ ቤጉ ፖሊስ መደበኛ ጨዋታ አንድ አቻ ተለያይተው አሸናፊውን ለመለየት ወደ መለያ ምት አምርተዋል
ቤጉ ሊግ የጥሎ ማለፍ ሻምፒዮና የፍፃሜ ውድድር
ወረዳ አንድ አኞንሾ ከ ቤጉ ፖሊስ
24/05/2026
የቤጉ ሊግ የጥሎ ማለፍ ውድድር የፍፃሜ ጨዋታ ዛሬ 9፡00 ላይ በወረዳ አንድ አኞንሾ እና ቤጉ ፖሊስ መካከል በአሶሳ ግብርና ኮሌጅ ይካሄዳል
24/05/2026
ባለሁለት እግሩ - ተመስገን ታምሩ
በቤጉ ሊግ ከተመለከናቸው ኮከብ ተጨዋቾች መካከል አንዱ የሆነው ተመስገን ታምሩ ለባምበሲ ቤልሚሊ እግርኳስ ክለብ ውጤታማነት አስተዋጽኦ ከነበራቸው ተጨዋቾች መካከል አንዱ ነው።
ተመስገን በቤጉ ሊግ የምድብ ጨዋታ 7 ግብና 5 ያለቀላቸው ኳሶችን በማቀበል ባምበሲ ቤልሚሊ ከምድቡ እንዲያልፍ ያደረገና በማጠቃለያ ውድድሩ 4 ግቦችን እና 4 ለግብ የሆኑ ኳሶችን በማመቻቸት ክለቡ የዋንጫ ባለቤት እንዲሆን አድርጓል።
ተመስገን በግራና በቀኝ መስመር አጥቂ እንዲሁም በአማካይ ቦታ መጫወት የሚችል ሁለቱም እግሩ ከኳስ ጋር የተዋሃደ ሁለገብ ተጨዋች ነው።
ተጨዋቹ በአንደኛ ሊግ ለሀደያ ሌሞ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ እንዲሁም ለማርቆስ ከነማ እና አምባ ጊዮርጊስ ክለቦች የተጫወተ ሲሆን በ2017 ለቡለን ከነማ እና በተለያዩ ሊጎች ተጫውቶ ያሳለፈ ጥሩ የአካል ብቃት እና ተከለ ሰውነት ያለው ተጨዋች ነው።
ተመስገን ከሜዳ ላይ ብቃቱ ባለፈ በስፖርታዊ ዲስፒሊን የተመሠከረለት ተጨዋች ነው።
ተመስገን በዚህ ብቃቱ የሚቀጥል ከሆነ የፕሪሚየር ሊግና ከፍተኛ ሊግ ክለቦች አይን ማረፊያ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ተመስገን አሁን ከባምበሲ ቤልሚሊ ጋር በክልል ክለቦች ሻምፒዮና ውጤታማ ለመሆን በዝግጅት ላይ ይገኛል።
መልካም ዕድል