26/08/2026
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሙስሊም ወጣቶች ካዉንስል የክረምት በጎ ፍቃድ አካል የሆነው የእግር ኳስ ዉድድር ሊጀመር ነው።
**********************
ውድድሩ በአሶሳ ከተማ በሚገኙ በተመዘገቡ አስር መስጂዶች መካከል የሚደረግ ሲሆን የዕጣ ማዉጣት ሥነ ሥረዓቱ በዛሬው ዕለት ተካሂደዋል።
ይህ የሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የክረምት በጎ ፈቃድ አካል የሆነው የእግር ኳስ ዉድድር ቅዳሜ ነሃሴ 23/2018 በአሶሳ መለስተኛ ትምህርት ቤት ሜዳ ይጀምራል።
በመክፈቻውም አቡበከር መስጂድ vs ሀሊድ ብን ወሊድ መስጂድ መካካል ከቀኑ 7 ሰአት የሚጀምር ይሆናል።