14/03/2026
የጨዋታ 236 ውጤት !
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Hawassa city sport club 0ffical page ሀዋሳ ከተማ ስፖርት ክለብ ህጋዊ ድረገፅ, Professional Sports Team, Awassa.
Welcome to Hawassa city sport club official face book page 💙
🏆🏆 1996 & 1999🏆🏆
Ethiopian premier league champions
1997 🏆
Ethiopian cup champions
Est1970
14/03/2026
የጨዋታ 236 ውጤት !
10/03/2026
የ2018 CBE የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 23ኛ ሳምንት ጨዋታ ውጤት
ሀዋሳ ከተማ 1 - 0 መቐለ 70 እንደርታ
75' ሽመልስ በቀለ
ሀይቆቹ ዛሬ የዓመቱን11ኛ ድላቸዉን ሲያስመዘግቡ ከዛሬው ድል በኋላ ነጥባቸዉን 40 ነጥብ እና 12 ንጹህ ጎል በማድረስ ከመሪዉ ሲዳማ ቡና ጋር ያላቸዉን የ ነጥብ ልዩነት በ 2 ዝቅ በማድረግ በ2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡
💙💙 እንኳን ደስ አላችሁ ሀይቆቹ 💙💙
💙 ድል እና ድምቀት ለሀይቆቹ 💙
10/03/2026
የ2018 CBE የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 23ኛ ሳምንት ጨዋታ
ሀዋሳ ከተማ - መቐለ 70 እንደርታ
10:00
ድል እና ድምቀት ለሀይቆቹ 💙💙💙
06/03/2026
ሐይቆቹ ግብ ጠባቂ አስፈረሙ - ሶከር ኢትዮጵያ አድናን ረሻድን ለማስፈረም የተቃረበው ሀዋሳ ከተማ የቀድሞው ተጫዋቹን አስፈረመ በዘንድሮ የውድድር ዓመት ከወትሮ በተሻለ ሁኔታ በዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚገኘው ሀዋሳ ከተማ በአጋማሹ .....
06/03/2026
ሀይቆቹ አጥቂ ለማስፈረም ተቃርበዋል - ሶከር ኢትዮጵያ ሀዋሳ ከተማዎች የዝውውር መስኮቱ የመጀመሪያ ፈራሚያቸው ለማግኘት ተቃርበዋል በቅርቡ ከሸገር ከተማ ጋር በስምምነት የተለያየው አጥቂው ማረፊያው ሀይቆቹ ቤት ለመሆን ተቃርቧል፤ ወደ ሀ...
05/03/2026
ሪፖርት| ሲዳማ ቡና ድል ሲቀዳጅ ተከታዩ ሀዋሳ ከተማ ነጥብ ጥሏል - ሶከር ኢትዮጵያ በአዳማ በተደረጉ ጨዋታዎች ሲዳማ ቡና ፋሲል ከነማን 1 ለ 0 ሲረታ ወላይታ ድቻ እና ሀዋሳ ከተማ 1 ለ 1 ተለያይተዋል ሲዳማ ቡና ከ ፋሲል ከነማ በዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ዐፄዎቹ…
05/03/2026
የጨዋታ 217 ውጤት !
28/02/2026
የደረጃ ሰንጠረዥ ከ21ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በኋላ !
28/02/2026
የጨዋታ 208 ውጤት !
22/02/2026
የ2018 CBE የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር 20ኛ ሳምንት ጨዋታ ውጤት
ሀዋሳ ከተማ 1 - 1 ድሬዳዋ ከተማ
61' ሽመልስ በቀለ 18' ድልአዲስ ገብሬ
ሃይቆቹ ከ 20 ጨዋታ 10 ጨዋታ በማሸነፍ እንዲሁም 6 ጨዋታ አቻ ወጥተዉ እና በ 4 ጨዋታ ሽንፈት ገጥሟቸዉ በ 36 ነጥብ እና በ 12 ንፁህ ጎሎች 1ኛ ደረጃ በመሆን ፕሪምየርሊጉን መምራት ጀምረዋል ፡፡ ሃይቆቹ በቀጣይ ሳምንት 21ኛ ሳምንት ጨዋታ በ ሮዱዋ ደርቢ ሲዳማ ቡናን የሚገጥሙ ይሆናል ይኼም ጨዋታ በጣም በጥቂት ነጥብ ልዩነት በደረጃዉ አናት ላይ ቁጭ ብለዉ መገናኘታቸዉ ከአሁኑ በጣም ተጠባቂ ጨዋታ አድርጎታል፡፡
16/02/2026
የሐዋሳ ከተማ ስፖርት ክለብ የ2018 በጀት ዓመት የግማሸ ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት ገመገመ።
13/02/2026
የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የጥር ወር ምርጥ አሰልጣኝ
ማግኘት ከሚገባቸው አስራ አምስት ነጥቦች አራቱን ብቻ ጥለው አስራ አንድ ነጥቦች ያሳኩት ሀይቆቹ በጥር ወር በተካሄዱ ጨዋታዎች ላይ ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ፣ በርካታ ግቦች በማስቆጠር እንዲሁም ዝቅተኛ የግብ መጠን በማስተናገድ (በጣምራ) ቀዳሚ ናቸው።
የቅርብ ተፎካካሪያቸው ነጌሌ አርሲን ጨምሮ በሰንጠረዡ የላይኛው ክፍል የሚገኙትን አዳማ ከተማና ኢትዮ ኤሌክትሪክን በተመሳሳይ ሁለት ለባዶ አሸንፈው ከኢትዮጵያ ቡናና ባህርዳር ከተማ ጋር ነጥብ የተጋሩት ሐይቆቹ በጥር ወር አስደናቂው ጉዞ ካደረጉ ክለቦች በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ።
የአሰልጣኝ ተመስገን ዳና የጨዋታ ዕቅድ እንዲሁም ውጤት ቀያሪ የነበሩ ውጤታማ ቅያሪዎችና ውሳኔዎች ደግሞ በ14ኛው ሳምንት ከመሪው ሲዳማ ቡና በአራት ነጥብ ርቀት ላይ የነበረውን ቡድን ወደ ዋንጫ ተፎካካሪነት በማብቃት ረገድ የላቀ አስተዋጽዖ አድርጓል።
በአምስት ጨዋታዎች ሰባት ግቦችን አስቆጥሮ አንድ ግብ ብቻ ያስተናገደ በማጥቃቱም ይሁን በመከላከሉ ረገድ ሁለንተናዊ ጥንካሬ የተላበሰ ድንቅ የመልሶ ማጥቃትና የፈጣን ሽግግር ቡድን ያዋቀሩት አሰልጣኙ ጠንካራ ቡድኖች በገጠሙባቸው መርሐ ግብሮች ላይ ሽንፈት ሳያስተናግዱ ትልቅ ዋጋ የሚሰጣቸው ድሎች ማስመዝገባቸው እንዲሁም ለውጤቱ መገኘት ባበረከቱት የጎላ ድርሻ በጥር ወር ድንቅ አፈፃፀም የነበራቸው አሰልጣኝ ያደርጋቸዋል።
በዚህ መሰረት ዕጩ ሆነው ከቀረቡት አሰልጣኝ ቱሉ ደስታ እና አሰልጣኝ ሙሉጌታ ምሕረትን በሶከር ኢትዮጵያ ኤዲቶሪያል እና በተሳታፊዎች ድምር ድምፅ በመብለጥ የወሩ ምርጥ አሰልጣኝ ሆነው ተመርጠዋል።
ከሶከር ኢትዮጵያ ኤዲቶሪያል ያገኙት ድምፅ - 100%
ከተሳታፊዎች ያገኙት ድምፅ - 43%