Ethio runners

Ethio runners

Share

An official social media Page Athletic news, Biography Writing, Analysis and reporting

Provide updated Athletic news
Athletic Biography Writer
Athletic Sport Analysis/Writer
Athletic Sport Reporter

05/12/2026

ልብ ሰባሪ አሳዛኝ ዜና !!
አትሌት የብርጓል መለስ በድንገት ከዚህ አለም ድካም አረፈች!!
አትሌቷ የሁለት ልጆች እናትም ነበረች!!
የ5 አመት ልጅ እና የ3 አመት ልጅ እናት የሆነችው የማራቶን አትሌቷ የብርጎል መለስ ህይወቷ እስካለፈበት ሰዓት ድረስ የአለማችን 91ኛዋ ፈጣን የማራቶን አትሌት ነበረች 54 ኢንተርናሽናል ውድድሮችን አድርጋ 3 ጊዜ ሀገሯን የወከለችው የብርጓል መለስ በ2013 በፖላድ በተካሄደው የአለም ሀገር አቋራጭ ውድድር በቡድን ሀገራችን የብር ሜዳሊያ ስታገኝ የብድኑ አባል ነበረች።

በአለማችን ላይ በሚታወቁ ትላልቅ ማራቶኖች እና ግማሽ ማራቶኖች ላይ ከፊት የማናጣት ጀግናዋ አትሌት የብርጓል መለስ ከቅርብ ጊዜ ወዲይ በልምደ ላይ ድንገት ስልምልም ብሎ የመወደቅ አደጋ በተደጋጋሚ እያገጠማት እንደነበረና ዛሬም በዚሁ አይነት ሁኔታ ህይወቷ እንዳለፈ ለማረጋገጥ ችያለሁ።

አትሌት የብርጓል መለስ ህይወቷ እስካለፈበት ሰዓት ድረስ በጎዳና ላይ ሩጫዎች ትታወቅ ነበረ ያረገጣቻቸው የአለማችን ጎዳናዎች አልነበሩም።

22 ማራቶኖች
19 ግማሽ ማራቶኖች
5 ጊዜ 10k በመሮጥ የምታወቅ ሲሆን ትራክ የሮጠችው 2 ጊዜ በ10,000ሜ ብቻ ነበረ ቀሪ የሀገር አቋራጭ ውድድሮች ናቸው። ጠቅላላ ውድድሮቿን ከ75 % በላይ በደረጃ የጨረስ ጠንካራ አትሌት ነበረች።
1 ሜትር ከ64 ሳ ሜትር ቁመት
55 ኪሎ ግራም ትመዝን የነበረችው ጀግናዋ አትሌት የብርጓል 37ኛ አመት ሊሞላት 24 ቀን ሲቀር ከዚህ አለም ድካም አርፋለች።
ነፍስ ይማር!!

05/12/2026

ጀግናዋን እስኪ በአንድ ቃል ግለፆት?

New women-only world record of 2:15:41. She successfully defended her title,

ሼር ላይክ በማድረግ ጀግኖችን እናበረታታት!!

05/11/2026

በዚህ ሳምንት ከፍተኛ የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌደሬሽን አመራሮች፦ የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌደሬሽን (World Athletics) ዋና ሥራ አስፈፃሚ (CEO) ወደ ኢትዮጵያ ሊመጡ ነው ይላል ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ገፅ ያገኘነው መረጃ

በዚህ ሳምንት ከሚመጡት ከፍተኛ የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌደሬሽን አመራሮች፦ውስጥ

1. ጆን ሪጅን - የዓለም አትሌቲክስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ

2. ማርክ ሁርስት - የዓለም አትሌቲክስ የጨረታ፣ የውድድር እና የዝግጅት ክፍል ኃላፊ

ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት በአዲስ አበባ በመገንባትና በመስፋፋት ላይትን የአትሌቲክስ መሠረተ ልማቶችን ይጎበኛሉ ይላል መረጃው

በተጨማሪም ኢትዮጵያ በቀጣይ ልታስተናግዳቸው በጠየቀቻቸው ዓለም አቀፍ ውድድሮች ዙሪያ ከተለያዩ የመንግሥት እና የፌደሬሽኑ አመራሮች ጋር እንደሚወያዩ ፌደሬሽኑ ገልፆል ።

ይህ ጉብኝት ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ አትሌቲክስ መድረክ ያላትን ከፍተኛ ስፍራ የሚያጠናክር እና ወደፊት ትልልቅ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ ያላትን አቅም የሚያሳይም ነው ተብሏል።
Photo google

05/11/2026

የመክፈቻው ፕሮግራም በከፊል !
የአፍሪካ አትሌትክስ ሻፒዮና በጋና አክራ ነገ ይጀመራል!!

05/11/2026

እስኪ ከሩጫ ወሬ ወጣ ልበልና የሆነ የሚገርምም፤ የሚያስተምርም ፤የሚያስቅም ፤ እውነት፤ ነገር ላውጋችሁ ፤ ኮንዶሚኒየም ቤት ተመዝግቤ ሳይደርሰኝ
3 ጠቅላይ ሚኒስተር እና 6 ከንቲባ ተቀያየረ ።

ኮንዶሚኒየም ቤት ለማግኘት ገና በልጅነት በ20 ያዎቹ መጀመሪያ እድሜ እያለሁ ተመዝግቤ ነበረ

አስታውሳለሁ ወያኔ ለ1997 ምርጫ ቅስቀሳ እንዲረዳው በ1996 ወደ መጨረሻ አመት አካባቢ ቤት እሰራለሁ ተመዝገቡ አሉን
እኛም በ1996 ሰኔ ወር ተመዝገብን ፤ በየጊዜው እጣ ተብሎ ሲወጣ ሳይደርሰኝ 2005 ዓ ም ላይ ደረስን።

ሌሎች ቤት ፈላጊ ጠያቂዎች ስለበዙ ተብሎ በ2005 ዓ ም የ1997 ተመዝጋቢዎች ቅድሚያ ይሰጣል ተብለን በ1997 የተመዘገባችሁበትን ቢጫ ካርድ ያዙ እንደገና ከ2005 ተመዝጋቢዎች ጋር ተመዝገቡ ተባልን።

ወደ ቀበሌ ሄድኩ
ቀበሌ ገብቼ መዝጋቢዋን ሳነጋግር
የ1997 ተመዝጋቢዎች ላይ ስምህ አለ
ባለ አንድ መኝታ ቤት ይላል አለችኝ
አዎ አልኳት።

ግን አሁን የምፈልገው ባለ ሁለት መኝታ ነው ምክንያቱም በ1996 ስትመዘግቡኝ ቤቱ በ2 አመት ውስጥ ይሰጣል ስለተባለ ገንዘቡን ላላገኝ እችላለሁ በሚል ነው ባለ 1 መኝታ የተመዘገብኩት።

9 አመት እንደምቆይ ባውቅ ኖሮ ባለ ሁለት መኝታ አድርጌ እመዘገብ ነበረ ስለዚህ የእኔ ችግር አይደለም ቀየሪልኝ አልኳት?

እሷም ባለ 2 መኝታ ከፈለክ በ2005 ከሚመዘገቡት ጋር አዲስ ተመዝጋቢ ላይ እንደ አዲስ መመዝገብ ትችላለህ ፤ ቅድሚያ እፈልጋለሁ ካልክ ደግሞ በነባር ምዝገባህ በ1997 መዝገብህ መቀጠል ትችላለህ ምርጫው የአንተ ነው አለች ።

ቀስ ብዬ ወያኔ እኮ ከ1983 በፊት ጫካ ነበረ አሁን ላይ ቤተመንግስት ነው ለውጥ ነው

የእኔም ህይወት ልክ እንደ እነሱ ባይሆኑም በመጠኑም ቢሆን ተቀይሯል ስለዚህ ባለሁለት መኝታ አድርጊልኝ አልኩ እየሳቀች አይቻልም አለችኝ።

ወስን አለች

ባለ አንድ መኝታ ቤት ተመዝግቤ 9 አመት ከጠበኩ፤ አዲስ ባለሁለት ተመዝጋቢ ሆኜ ስንት አመት ልጠብቅ ነው? አልኩና
በ1996 (97) መዝገብ እቀጠላለሁ አልኩ ቀጠልኩ። ወረቀት ፕሪንት አድርጋ ሰጠችኝ።

ወያኔ ስልጣን እስኪያስረክብ ድረስም እጣ ሲወጣ ሳይ ሳይ ሳይ ስሜ የለም።

ከዚያም አንዱ የማውቀው
ወንዴ
አልደረሰህም አለኝ

አዎ አልኩት

ከአንተ ጋር የተመዘገቡ እኮ ጠቅላላ ደርሷቸዋል

ወንዴ ምንድ ነው?

ወደ ቀበሌ አካባቢ ተፍ ተፍ አትይም?
"አባል" የሚባል ነገርም አለ ?

እሱን ከሞከርሽ "ፍቱን" ነው
"ኮንዶው" ወዲያው ከቺ ነው አለኝ

ብሮ ይቅርብኝ። አልፈልግም።

ሌላም ሰው በዚህ ጉዳይ አነጋግሮኛል አልፈልግም አልኩት ።

አንዱ ሙደኛ ልጅ ደግሞ ምን ቢለኝ ጥሩ ነው

ወንዴ ስም ቀይሪ

በክርስተና አባትሽ አድርጊው

ባልገባው ሙድ ሆኜ

ምን አልኩት?

ስምሽ
አደር ስኮር ይኑረው
ለማለት ነው አለኝ
ተሳስቀን ተለያየን።

ይሄኛውም የብልፅግና መንግስት መጣ ከመጣ በኋላ ቤት ሰጥቶ ያበለፅገኛል ይደርሰኛል ስል ስል ሳይደርሰኝ በመጠባበቅ እያለሁ ከ2 አመት በፊት ይመስለኛል ከንቲባዋ የ1997 ቤት ተመዛጊቦች አዳርሰን ጨርሰናል አለች ተባለ ወይ ጉድ አልኩ?

ቁጠባ ከተጀመረ ጀምሮ አላቋረጥኩም ሳይደርሰኝ ደርሶሀል የሚል ከንቲባ ደግሞ መጣ ?
የተሳሳተ መረጃ ሰጥተዋት ይሆናል እንጂ እንዴት? አልኩ?

አሁን ላይ ደግሞ ምን አዲስ ነገር እንዳለ (እንደተፈጠረ ) ባላውቅም
ወሬው ሁሉ ስለ ኮንዶሚኒየም ቤት ነው ።

የሚገርመው እንደ እኔ ግራ የገባቸው የ2005 ኮንዶሚኒየም ቤት ተመዝጋቢዎች 14ሺህ ተከታይ ያለው የፌስቡክ ገፅ ከፍተው መረጃ ይለዋወጠሉ።

እኔ የ1997 ተመዝጋቢ ስለሆንኩ እራሴን አላሳንስም በማለት ላይክም አላደረኳቸውም ማውራትም አለፈለኩም።

በኋላ እንደ እኔ ቤት ያልደረሳቸው ተሰባስበው ቤቶች ኤጀንሲ ሄደው አመለከቱ መሰለኝ በኋላም በስህተት ነው ተባለ መሰለኝ የ97 እንዳላለቀ ሰማሁ ተመስገን አልኩ!

በኋላም አንዱ ወዳጄ ይሄን ስማው ብሎ ይሄን የፖሰትኩላችሁን ቪዲዮ ላከልኝ ስሙት

መልካም ዜና ይሆናል በሚል
በ22 አመት ቤት ጠብቀን ልናገኝ ይሆናል ብዬ ሰማሁት
ስሰማው

ስለ ቅድሚያ የተመዘገቡ ማዳረስ አላማዳረስ
ማብራሪያ የለውም
በየጊዜው ስላለው የቤት ፍላጎት መጨመር
ተናግረው
የሌሎች ያደጉ ሀገሮች የቤት እጥረት ተሞክሮን እያጣቀሱ

"ሁሉንም ማዳረስ አይቻልም"

ሲሉ ተስፋ ቆረጥኩ።

ግን ደግሞ ተፅናናሁ ያው
እሳቸውም ሆኑ እነዚህ ከታች
ስማቸውን የዘረዘርኳቸው በሙሉ ከእኔ በኋላ ተመዝጋቢ ናቸው ብቻዬን ቤት አላጣሁም በሚል
እንደመፅናናትም አደረገኝ።

እኔ ቤት ተመዘግቤ በመጠበቅ ላይ እያለሁ የተቀያየሩ ከንቲባዎች

አርከበ እቁባይ (1998 - 2003) እኚህ በወቅቱ ከንቲባ ስለነበሩ በሳቸው ዘመን ስለተመዘገብኩ ቀድመውኝ ተመዝግበው ወስደው ሊሆን ይችላል መረጃው የለኝም።ሌሎቹን ግን እቀድማለሁ ።

ብርሀኑ ደሬሳ January 2003
May 2006) ነበሩ እቀድማቸዋለሁ

ኩማ ሚደቅሳ May 2006 -
October 2008 ነበሩ እቀድማቸዋለሁ

ድሪባ ኩማ October 2008 -
July 2013) ነበሩ እቀድማቸዋለሁ

ታከለ ኡማ July 2018 - August 2020) ነበሩ እቀድማቸዋለሁ

አዳነች አበቤ 2020 ነው የመጡት እቀድማቸዋለሁ

ከአርከበ ውጪ የተዘረዘሩትን ሳይ እፅናናለሁ!!

ደግሞም እኮ !
ሰው ሚዛናዊ አይደለም
ፍትህ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው
ፍትህ ያጓደሉ የት እንዳሉ በአይኔ አይቻለሁ።
ለሁሉም ነገር እግዚአብሔር አንድ ቀን መልስ አለው ።
እኔ እኮ ድሮም ቤቴ በሰማይ ነው"
ብዬ መዘመርን ብቻ መረጥኩ።

ሰላም ሁኑ የዩቱብ ቻናሌን ተመልከቱልኝ
በቀላሉ ለማግኘት ዩቱብ ላይ ገብታችሁ ኢትዮራነርስ የሚለውን በእንግሊዘኛ አያይዛችሁ በመፃፍ ሰርች አድርጋችሁ ተመልከቱት ከወደደችሁት በተለይ የሩጫ ስፖርትን የምትወዱን ብቻ ከሆነ የራሳችሁን እርምጃ ውሰዱ።

ሰላም ሁኑ!!

05/11/2026

በፎቶው ላይ ከምትመለከቷቸው ውስጥ በ2021 ኬኒያ ላይ በተካሄደው U20 ኢትዮዽያን ወክለው ወርቅ ካስገኙት አትሌቶች እነማንን ያስታውሳሉ?

Photos from Ethio runners's post 05/11/2026

በቅርቡ የተሞሸረው አትሌት ቦኬ ድሪባ በማራቶን አሸነፈ!!
በሞሮኮ ራባት በተደረገ የማራቶን ውድድር በወንድም በሴትም ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አሸንፈዋል።
በሞሮኮ ራባት በተደረገ የማራቶን ውድድር ነው በቅርብ ከአትሌት ሲንቦ አለማየሁ ጋር የተሞሸረው ቦኬ ድሪባ አሸናፊ የሆነው።
በሴቶች ከ3 አመት በኋላ ወደ ውድድር የተመለችው የ32 አመቷ አለምፀሀይ አሰፋ አሸናፊ ሆናለች።

MEN:
1. Boki Diriba 2:07:52
2.Tolcha Tefera 2:08:27
3. Chalu Deso 2:08:28

WOMEN:
1Alemtsehay Asefa 2:25:03 2Meseret Abebayhu 2:25:42
3Siranesh Yirga 2:27

የተወሰኑ ፎቶዎች ከኤሊት አትሌት ገፅ ተጠቅመናል።

05/11/2026

ዛሬ የአትሌት ሀጎስ ገ/ህይወት ልደት ነው!!
አትሌቱ ኦሎፒያን ነው!!
የመስፍን ኢንጅነሪግ ክለብ አትሌት ነው!
አትሌቱ በኢንተርናሽናል ደረጃ 112 ውድድሮችን አድርጓል።
በተደጋጋሚ ብዙ የሮጠው 5000 ሜትርን ነው 57 ጊዜ ሮጣታል።

በ5ሺ ሜ የምንጊዜም የዓለማችን ፈጣን ባለሰዓቶች ውስጥ ያለው ደረጃ ስናይ፦ የዛሬ 2 አመት በ30 ሜይ 2024 በኖርዌይ ኦስሎ ያስመዘገበው
12:36.73 NR ሰዓቱ በ2ኛ ደረጃ ላይ እንዲቀመጥ አድርጎታል።

➙ 18 ጊዜ ሀገሩን ወክሏል።
በሀገር ውክልና ውድድር ማለትም በኦሊምፒክ ፤ በአለም የአትሌትክስ ሻምፒዮና ፤ በወጣቶቸ ሻንፒዮና ፤ በሀገር አቋራጭ ውድድሮች እንዲሁም በአፍሪካ ሻንፒዮናዎች በጠቅላላው 3 ወርቅ 1 ብር 2 ነሀስ በቡድን 2 ወርቅ በጥቅሉ 8 ሜዳሊያዎችን ለሀገሩ አስገኝቷል።

አንድ አትሌት በሩጫ ዘመኑ ሊያሳካ ከሚገባው አንዱና ዋናው በኦሊምክ ጨዋታዎች ላይ መሳተፍና ሜዳሊያ ማጥለቅ ነው ይህ አትሌት በኦሊምፒክ ተሳትፎው በ2016 በሪዮ ኦሎፒክ በ5000ሜ የነሀስ ሜዳሊያ አጥልቋል።

ኢትዮራነርስ ለኦሊምፒክ ጀግኖች ትልቅ ክብር አለው!

ዛሬ የጀግናው አትሌት ሀጎስ ገ/ህይወት ልደት ነው። አትሌቱ በዛሬዋ ቀን እ ኤ አ 11 May 1994 ዓ ም ተወለደ። 32 አመት።

Happy Birthday!
መልካም ልደት!
እንኳንም ተወለድክ!!

የሀጎስ አድናቂ የሆነችሁ በሙሉ እስኪ እንኳንም ተወለድክ በሉት!!
ሀጎስ ልደቱን ሲያከብር የሚያሳይ ቪዲዮ ዮቱባችን ላይ ተጭኗል ሰብስክራይብ አድርገው ይመልከቱ።






ሼር ብቻ!

05/11/2026
05/10/2026

የአትሌቶች የቪዛ ጉዳይ መፍትሔው ምንድን ነው?
በዚህ ጉዳይ ይረፋ ብርሀኑ የተሰጠ የመፍትሄ ሀሳቦች!!
ኮመንት ላይ ይመልከቱ

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Denver?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Telephone

Address


111 N Patsburg Street
Denver, CO
80018